ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የማሳ ላይ እንክብካቤ ስራዎችንና የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ከወትሮው በተለዬ ሁኔታ ተግባራዊ ማድረግ ይገባል ፦አቶ አጥናፉ ኃይሌ
በካፋ ዞን ገዋታ ወረዳ የግብርና ምርትና ምርታማነት ዕድገት ለብልፅግናችን በሚል መሪ የንቅናቄ መድረክ ተካሂዷል። ምርትና ምርታማነትን ከማሳደግ ባሻገር ሊታረስ የሚችሉ ሰፊ መሬቶችን በመለየት የማሳ ሽፋን ስራዎችን ማሳደግ እንደሚገባ በመድረኩ የተገኙት የካፋ ዞን የብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አጥናፉ ኃይሌ ተናግረዋል። ወቅታዊ የግብርና ስራዎች እንዲሳኩ አመራሩና ባለሙያው ለአርሶ አደሩ የሚያደርገውን ሙያዊ ዕገዛ የበለጠ ማጎልበት ይገባቸዋል ብለዋል፡፡…
