Trendings

በበጀት ዓመቱ በሁሉም የሀገሪቱ ክልሎች 30 ሚሊዮን ዜጎችን ለማመካከር እቅድ ይዞ እየሠራ እንደሚገኝ የሠላም ሚኒስቴር አስታወቀ።

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በሚዛን አማን ከተማ በማህበረሰብ ተኮር ምክክር ዉጤታማነት ዙሪያ በሠላም ሚኒስቴር አማካይነት ለተከታታይ ሁለት ቀናት ሲሰጥ የቆየዉ የአሰልጣኞች ስልጠና ተጠናቋል። በደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ከ6ቱም ዞኖች ለተወጣጡ የሠላምና ጸጥታ ተቋም ባለሙያዎችና የማህበረሰብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ሙያተኞች የአመቻችነት ሥልጠና እንዲወስዱ የተደረገ ሲሆን በቀጣይ ተግባራት ውጤታማነት ዙሪያም አቅጣጫ ተቀምጧል። የሥልጠናው ተሳትፊዎች በቆይታቸው በቂ…

Read More

የተቋሙን እቅድ ለማሳካት ሌት ከቀን የምንሰራበት ወቅት ነው ፦ ወ/ሮ ህይወት አሰግድ

የደምኢህክመ ገቢዎች ቢሮ የበጀት ዓመቱን ገቢ አሟጦ ለመሰብሰብ የሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ የምክክር መድረክ እያካሄደ ነው። ቢሮው የ2017 በጀት ዓመት የ10 ወራት የገቢ አሰባሰብና ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ በሚዛን አማን ከተማ እያደረገ ይገኛል። የቢሮው ኃላፊ ወ/ሮ ህይወት አሰግድ በምክክር መድረኩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት የታክስ ገቢ መንግስት የህዝቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፍላጎት ደረጃ በደረጃ ምላሽ…

Read More

በዳዉሮ ዞን ታርጫ ጠቅላላ ሆስፒታል በማኅጸን ውልቃት የሕክምና ዘርፍ እየተሰጠ የሚገኘው አገልግሎት በተሻለ ሁኔታ እንዲሰጥ ለማድረግ የተቀናጀ ርብርብ እንደሚጠይቅ ተገለጸ።

አገልግሎቱን የበለጠ ተደራሽ ለማድረግ የባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ ተግባሩ እየተመራ እንዳለም የሚመለከታቸው የሥራ ኃላፊዎች ተናግረዋል። በዳዉሮ ዞን የታርጫ ጠቅላላ ሆስፒታል በተለያዩ የሕክምና ዓይነቶች በሰለጠኑ ባለሙያዎች አገልግሎቱን ተደራሽ እያደረገ እንደሚገኝ ከሆስፒታሉ ያገኘነው መረጃ ያሳያል። በተለይም በማህጸንና ጽንስ፣ በሕጻናት፣ በአጥንትና ድንገተኛ አደጋዎች፣ በአጠቃላይ ቀዶ ጥገናና በውስጥ ደዌ በሽታዎች በስፔሻሊት ደረጃ የሕክምና አገልግሎቱ እየተሰጠ ይገኛል። ከእነዚህ አንዱ በሆነው በማኅጸንና…

Read More

ብዝኃነት የኢትዮጵያ ጌጥ እና ዐቅም ነው!

ብዝኃነት የኢትዮጵያ ጌጥ እና ዐቅም ነው! ኢትዮጵያ በሕዝቦቿ ብዝኃ ማንነት ደምቃ፣ ፀንታና ታፍራ የኖረች፣ ብዝኃ የተፈጥሮ ሀብት ባለቤት የሆነች ድንቅ ሀገር ናት፡፡ ብዝኃነታችን የጥንካሬያችን፣ የሥልጣኔያችን፣ የአይበገሬነታችን፣ የክብራችን፣ የነፃነታችን እና የአልሸነፍ ባይነታችን ምሥጢር ነው፡፡ በተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች የሚገኙ ጥንታዊ ሃይማኖታዊ እና ታሪካዊ ቦታዎች እና የኪነ ሕንጻ ሀብቶቻችን የብዝኃነታችን ውጤቶች ናቸው፡፡ የአክሱም ሐውልቶች፣ የጢያ ትክል ድንጋዮች፣ የላሊበላ…

Read More

በበጀት ዓመቱ በተለያዩ ዘርፎች የተሰማሩ 72 ትላልቅ ፋብሪካዎች ሥራ ይጀምራሉ -ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር)

በተያዘው በጀት ዓመት በተለያዩ ዘርፎች የተሰማሩ 72 ትላልቅ ፋብሪካዎች ሥራ እንደሚጀምሩ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የኢንዱስትሪ ዘርፍን በሚመለከት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በሰጡት ማብራሪያ÷በዘርፉ በተያዘው በጀት ዓመት 12 ነጥብ 8 በመቶ እድገት ይጠበቃል ብለዋል፡፡ ማኑፋክቸሪንግ ላይ 12 በመቶ እድገት እንደሚጠበቅ ጠቅሰው÷ኮንስትራክሽን ላይ ደግሞ 12 ነጥብ 3 በመቶ ገደማ…

Read More

ባለፉት አስር ወራት 301 ሺህ ዜጎች በህጋዊ መንገድ ወደ ውጭ ሀገራት የስራ ስምሪት አድርገዋል – የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል::

ባለፉት አስር ወራት 301 ሺህ ዜጎች ክብርና ደህንነታቸውን በጠበቀ መልኩ ወደ ውጭ ሀገራት የስራ ስምሪት ማድረጋቸውን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ። የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል የተያዘውን በጀት ዓመት ያለፉት ዘጠኝ ወራትን ዕቅድ አፈጻጸም አስመልክቶ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል። በተያዘው በጀት ዓመት መጀመሪያ የዘርፉ ባለድርሻ አካላትን በማካተት “ዓመተ-ምርታማነት” በሚል ስያሜ እያንዳንዱ ሥራዎች ወደ ውጤት…

Read More

የሐረሪዎች የጥበብና የእውቀት ውጤቶች ድንበር ተሻግረው የዓለማችን ህዝቦች የቅርስ ሀብት ሆነዋል – አቶ ቀጄላ መርዳሳ::

የሐረሪዎች የጥበብና የእውቀት ውጤቶች ድንበር ተሻግረው የዓለማችን ህዝቦች የቅርስ ሀብት ሊሆኑ በቅተዋል ሲሉ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ቀጄላ መርዳሳ ተናገሩ። በሐረሪ ክልል የሸዋል ኢድ በዓል የመክፈቻ መርሃ-ግብር ተካሂዷል። በመርሃ-ግብሩ ላይ የተገኙት የባህልና ስፖርት ሚኒስትር አቶ ቀጄላ መርዳሳ የሐረሪዎች የጥበብና የእውቀት ውጤቶች ድንበር ተሻግረው የዓለማችን ህዝቦች የቅርስ ሀብት መሆናቸውን ተናግረዋል። ሐረሪዎች ከደማቅ ታሪኮቻቸው ጎን ለጎንም የሰላምና የፍቅር…

Read More

አየር ኃይል የትኛውንም ግዳጅ ለመፈፀም በላቀ የዝግጁነት ደረጃ ላይ ይገኛል – ሌ/ጄ ይልማ መርዳሳ

አየር ኃይል የሚሰጠውን ማንኛውንም ግዳጅ ለመፈፀም በላቀ የዝግጁነት ደረጃ ላይ ይገኛል አሉ የኢፌዴሪ አየር ኃይል ዋና አዛዥ ሌ/ጄ ይልማ መርዳሳ፡፡ የአየር ኃይል ምክትል አዛዥ ለአየር ኦፕሬሽን በግዳጅ አፈጻጸም ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከቱ ክፍሎች እውቅና ሰጥቷል፡፡ ሌ/ጄ ይልማ መርዳሳ በዚህ ወቅት÷ተቋሙ የሚሰጠውን ተልዕኮ እና ግዳጅ ለመፈፀም በከፍተኛ የዝግጁነት አቅም ላይ እንደሚገኝ አረጋግጠዋል ። አየር ኃይል በአጭር ጊዜ…

Read More

የሚዲያ ተቋማት የንቃተ ህግ በማሳደግ ለፍትህ ተደራሽነት መረጋገጥ የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ ተጠየቀ።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፍትህ ቢሮ በፍትህ ዘርፍ ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ አፈጻጸም ዙሪያ በየደረጃው ከሚገኙ የሚዲያ እና የፍትህ ተቋማት ጋር በቦንጋ ከተማ ውይይት እየተካሄደ ይገኛል። በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የቢሮው ኃላፊ ወ/ሮ ቤተልሔም ዳንኤል፥ የፍትህ እና የሚዲያ ተቋማት ቅንጅት በማጠናከር በዘላቂነት የንቃተ ህግ እና የኅብረተሰብ ተሳትፎ ተግባራትን በማሳለጥ ለፍትህ ተደራሽነት መረጋገጥ ሚናቸውን መወጣት አለባቸው ብለዋል።…

Read More

ኢትዮጵያ ያዘጋጀችው ዓለም አቀፍ የሃይማኖት ተቋማት ኮንፈረንስ ዛሬ በአዲስ አበባ ተከፈተ

ኢትዮጵያ ያዘጋጀችው ዓለም አቀፍ የሃይማኖት ተቋማት ኮንፈረንስ ዛሬ በአዲስ አበባ ተከፍቷል። ይህንን ዓለም አቀፍ የሃይማኖት ተቋማት ኮንፈረንስ የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ፣ የሰላም ሚኒስትሩ አቶ ብናልፍ አንዱዓለም እና የመሀመድ ቢን ዛይድ ዩኒቨርሲቲ ቻንስለር ዶክተር ከሊፋ ሙባረክ ከፍተውታል። በኮንፈረንሱ ላይ ከ16 ሀገራት የተውጣጡ የሃይማኖት አባቶችና የተቋማት መሪዎች እየተሳተፉ ነው። ኮንፈረንሱ በልዩ ልዩ መርሀ ግብሮች እስከ ነገ…

Read More