Trendings

#ካንካርና_ኩችጓ

ባህል የአንድ ብሔረሰብ ማንነት መገለጫው፤ ትልቅ እሴቱ ነው። ባህልን ማልማት፣ ማሳደግ ለትውልድ ማሸጋገር ደግሞ የአሁኑ ትውልድ ትልቅ አደራው ነው። ይህ ትልቅ አደራ ሳይሸረፍ፣ሳይበረዝ የጥንት ይዘቱን ጠብቆ እንዲለማ ማድረግም ያስፈልጋል። በክልላችን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ከሚገኙ ብሔረሰቦች አንዱ የፃራ ብሔረሰብ ነው ። ብሔረሰቡ የራሱ የሆኑ ባህላዊ እሴቶች አሉት ።ከእነዚህ እሴቶች ውስጥ አንዱ ባህላዊ አለባበስና አጋጌጥ ተጠቃሽ ነው…

Read More

ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር ኢ/ር) በቦንጋ ከተማ የኮሪደር ልማት ስራ ምልከታ አደረጉ

በኮሪደር ልማት ምልከታ ላይ የተገኙት ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ የቦንጋ ከተማ የኮሪደር ልማት ስራ እንቅስቃሴ በጥሩ ሁኔታ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል። ከተማው ለኑሮ ምቹ እና ሳቢ እንዲሆን አየተሰራ የሚገኘውን የከተማ ኮርደር ልማት ለማሳለጥ ህብረተሰቡ ወስን ከማስከበር ረገድ እያደረገ ያለው ርብርብ እጅግ የሚመሰገን ነው ብለዋል። ከተማው ሰፊ በመሆኑ ስራውን በውጤታማነት ለመምራት እንዲቻል በየደረጃው ከፋፍሎ የቅድሚያ…

Read More

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በበልግ ግብርና ስራዎች የቴክኖሎጂ አጠቃቀም እየተሻሻለ መምጣቱ ተገለጸ ፡

በ2016 የበልግ አዝመራ ወቅት በክልሉ ከ354 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል ፡፡ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ለግብርናው ዘርፍ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ ወደ ተግባራዊ እንቅስቃሴ በመገባቱ የተሻለ አፈጻጸም እየታየ ነው ፡፡ ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የአፈር ማዳበሪያና የምርጥ ዘር አቅርቦት መሻሻሎች እንዳሉት ያነጋገርናቸው አርሶ አደሮች ተናግረዋል ፡፡ በቤንች ሸኮ ዞን በሰብል አብቃይነቱ ከሚታወቁት…

Read More

የዘንድሮ “ማሽቃሬ ባሮ” በድርርብ ስኬቶች እና ደስታዎች የታጀበ ነው:- አቶ እንዳሻው ከበደ

የ2018 ዓ.ም የካፈቾ ዘመን መለወጫ ማሽቃሮ በዓልን አስመልክቶ የካፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳሻ ከበደ መግለጫ ሰጥተዋል። በዓሉ ለዓመታት መከበር ካቆመ በኃላ በ1986 ዓ.ም የባህል እና ቋንቋ ስምፖዚዬም መካሄዱን ተከትሎ በ1998 ዓ.ም በድጋሜ መከበር መጀመሩን ያወሱት ዋና አስተዳዳሪው ዘንድሮ በልዩ ድምቀት ድምቀት ለማክበር ዝግጅት መደረጉን ገልጸዋል። በዓሉ ህዝባዊ መሠረት ያለው በመሆኑ ላለፉት 20 ዓመታት ወቅቱ…

Read More

በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 10ኛ መደበኛ ስብሰባ የምክር ቤቱ አባላት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ካነሷቸው ጥያቄዎች፡-

የዘንድሮ ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ነፃ፣ ፍትሃዊና በመላ ኢትዮጵያውያን ዘንድ ተዓማኒ እንዲሆን እንዲሁም በጸጥታ ችግሮች ምክንያት እንዳይስተጓጓል በመንግሥት በኩል ምን እየተሰራ ነው? በትግራይ ክልል ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን የፕሪቶሪያውን ስምምነት ትልቅ ተስፋን የጫረ ቢሆንም አሁን ላይ በሕወሓት ቡድን ምክንያት በክልሉ ውስጥ ሥርዓት አልበኝነት እንዲነግስና የግጭት ድባብ እያንዣበበ ይገኛል፤ የክልሉ አሁናዊ የሰላም ሁኔታ በምን ደረጃ ላይ ይገኛል? የትግራይ…

Read More

ሁሉን አካታች የሰላም ግንባታ እንዲኖር በትኩረት ይሰራል – ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር)

ሴቶች፣ ወጣቶችና ተጋላጭ የማህበረሰብ ክፍሎች በሀገር ሰላም ግንባታ ያላቸውን ሚና የበለጠ ለማጠናከር እንደሚሰራ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ(ዶ/ር) ገለጹ። “ሰላምን ተለማመዱ በሰላም ኑሩ” የተሰኘ ፕሮጀክት ይፋ ሆኗል። ኤርጎጌ ተስፋዬ(ዶ/ር) በዚህ ወቅ እንዳሉት÷ሴቶች፣ ወጣቶችና ተጋላጭ የማህበረሰብ ክፍሎች በሰላም ግንባታ ሒደት ላይ እንዲሳተፉ እየተሰራ ነው። ሰላምን በመገንባት ሥራ የአመራር ሚና እንዲኖራቸው ትኩረት መደረጉን ጠቁመው÷ማህበራዊ ትስስርን ማጠናከር…

Read More

መልካም አስተዳደር ለማስፈን በየደረጃው የሚገኙ ምክር ቤቶች ተቀናጅተው ሊሠሩ እንደሚገባ ተገለጸ።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የክልልና የዞን ምክር ቤቶች 5ተኛ ዙር የጋራ ምክክር ፎረሙ በሁለተኛ ቀን ውሎ የተመረጡ የዞን ምክር ቤቶች የ2017 በጀት ዓመት የ6 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ለፎረሙ አባላት ቀርቦ ተወያይተውበታል። በዚህ ወቅት የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ ወንድሙ ኩርታ እንደገለጹት በክልሉ የሚገኙ ምክር ቤቶች በየ ደረጃው የሚስተዋለውን…

Read More

የሸካቾ ብሄረሰብ የባህላዊ አስተዳደር መዋቅር መሪ በዓለ ስመት ተካሄደ።

የሸካቾ ብሄረሰብ የባህላዊ አስተዳደር መዋቅር ንግሥና ስነስርዓት በሸካ ዞን የነገሥታት መናገሻ በሆነችሁ ጥንታዊቱ የአንድራቻ ወረዳ ጌጫ ከተማ ተካሂዷል። በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ካሉት ስድስት የአስተዳደር መዋቅሮች አንዱ የሆነው የሸካ ዞን የድንቅ ተፈጥሮ፤ የብዙ ታሪክና ባህላዊ ዕሴት ባለቤት የኾነ ዞን ነው። “ባህላችን ለአብሮነታችንና ለዘላቂ ሰላማችን” በሚል መሪ ቃል በተካሄደዉ የሸካቾ ብሄረሰብ የባህል ሲምፖዚየም የተለያዩ ኩነኔቶች…

Read More