የብልፅግና ፓርቲ 2017 ዓ.ም በጀት ዓመት የ6 ወራት የስራ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ መካሄድ ጀምሯል።
በአጠቃላይ ሀገራዊ ፓለቲካ ሁኔታ፣ ጠንካራ ፓርቲ ግንባታ ለማሳካትና በፓርቲና በመንግሥት ቅንጅት የሚሰሩ የንቅናቄ አጀንዳዎችን የሚገመግመው መድረክ በብልፅግና ፓርቲ ዋና ፅ/ቤት ተጀምሯል። በመርሀ ግብሩ ላይ የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት ክቡር አቶ አደም ፋራህን ጨምሮ የብልፅግና ፓርቲ ዋና ፅ/ቤት የዘርፍ አመራሮች የክልል ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ኃላፊዎች እንዲሁም የክልል የአደረጃጀት እና የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። ለ3 ተከታታይ ቀናት ይካሄዳል…
