Trendings

የኢትዮጵያ ሴቶች ለሀገራቸው የላቀ አበርክቶ አድርገዋል – ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ

ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን በማስመልከት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። ፕሬዝዳንት ታዬ ቀኑን በማስመልከት በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት የኢትዮጵያ ሴቶች ለሀገራቸው ነፃነት፣ የኢኮኖሚ ዕድገት፣ ማህበራዊ እሴቶችና ባህሎችን ለማፅናት ያበረከቱት አስተዋጽኦ የላቀ ነው ብለዋል። እንቅፋቶችንና ጎታች እሳቤዎችን በመጣል፣ በመላ አቅማቸው የኢትዮጵያን የመዘመን መንገድ ዋነኛ መሪና ተዋናይ መሆናቸውንም ገልጸዋል። ዘንድሮ ቀኑ በዓለም አቀፍ ደረጃ…

Read More

በ6 ዓለም አቀፍ መዳረሻዎች ሙሉ በሙሉ በሴቶች ብቻ በረራ ተደረገ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ትናንት ከምሽቱ 5 ሠዓት ጀምሮ በሥድስት ዓለም አቀፍ መዳረሻዎች ሙሉ በሙሉ በሴቶች ብቻ በረራ ማድረጉ ተገለጸ፡፡ ይህን ተከትሎም የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን የኤርናቪጌሽን አገልግሎት ዘርፍ እነዚህን ሥድስት ዓለም አቀፍ በረራዎች በሴቶች ብቻ እንዲስተናገዱ ማድረጉን በማኅበራዊ ትርሥሥር ገጹ አስታውቋል፡፡ በረራዎቹ በሴቶች ብቻ እንዲሸፈኑ የተደረገው፤ ዓለም አቀፉን የሴቶች አስመልክቶ መሆኑም ተገልጿል ሲል ኤፍ ኤም…

Read More

ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የማሳ ላይ እንክብካቤ ስራዎችንና የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ከወትሮው በተለዬ ሁኔታ ተግባራዊ ማድረግ ይገባል ፦አቶ አጥናፉ ኃይሌ

በካፋ ዞን ገዋታ ወረዳ የግብርና ምርትና ምርታማነት ዕድገት ለብልፅግናችን በሚል መሪ የንቅናቄ መድረክ ተካሂዷል። ምርትና ምርታማነትን ከማሳደግ ባሻገር ሊታረስ የሚችሉ ሰፊ መሬቶችን በመለየት የማሳ ሽፋን ስራዎችን ማሳደግ እንደሚገባ በመድረኩ የተገኙት የካፋ ዞን የብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አጥናፉ ኃይሌ ተናግረዋል። ወቅታዊ የግብርና ስራዎች እንዲሳኩ አመራሩና ባለሙያው ለአርሶ አደሩ የሚያደርገውን ሙያዊ ዕገዛ የበለጠ ማጎልበት ይገባቸዋል ብለዋል፡፡…

Read More

በክልሉ ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ አዘጋጅነት እየተካሄደ ያለው የስነ ጥበብና ኪነ ጥበብ ዉድድር በህሩት ምትኩ አሸናፊነት ተጠናቋል።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ያዘጋጀው ክልላዊ የኪነ- ጥበብ እና ስነ-ጥበብ ፈጠራ ውድድርና ትዕይንት በዳውሮ ዞን ታርጫ ከተማ ተካሂዷል። የክልሉ ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ባዘጋጀዉ ክልላዊ የስነ ጥበብና ኪነ ጥበብ ዉድድር ሚስ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ በመሆን ከቤንች ሼኮ ዞን ህሩት ምትኩ አሸንፋለች፡፡ በተመሳሳይ መልኩ በስዕል ዉድድር የከፋ ዞን ወክሎ የቀረበዉ…

Read More

በክልሉ የተረጋጋና ሰላማዊ የፖለቲካ አከባቢ በመፍጠር ለዜጎችና ለኢንቨስትመንት እንቅስቃሴዎች ምቹ ሁኔታዎች እንዲኖሩ እየተሠራ ነው፦ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)

የፌዴራል እና የክልል ምክር ቤቶች አባላት ከወከላቸው ሕዝብ ጋር ያደረጉትን ውይይትና የመስክ ምልከታ አስመልክቶ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) እና ሌሎች የክልሉ አስፈጻሚ አካላት በተገኙበት በቦንጋ ከተማ ግብረ መልስ ሰጥቷል ። የፌደራልና ክልል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በክልሉ በሁሉም ዞኖች በተለያዩ ወረዳዎች ከወከላቸው መራጭ ሕዝብ ጋር በሰላም፣ ልማትና…

Read More

በሚዲያ እና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ የመንግስት ዋና ዋና አጀንዳዎችን ከማስረጽ አንጻር ውጤታማ ስራዎች ተሰርተዋል

በበጀት አመቱ ግማሽ አመት እቅድ በሚዲያ እና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ የመንግስት ዋና ዋና አጀንዳዎችን ከማስረጽ አንጻር ውጤታማ ስራዎች መሰራታቸውን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ። የሚዲያ እና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ የግማሽ ዓመት እቅድ አፈጻጸም ግምገማ “ዓላማ ተኮር፤የተናበበ እና የተቀናጀ የተግባቦት ስርዓት ለእመርታዊ እድገት” በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ነው። በመድረኩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ከበደ…

Read More

በህብረተሰቡ ዘንድ የሚነሱ የልማት ጣያቄዎችን ለመመለስ መንግሥት እያደረገ ያለው ጥረት አበረታች ነው

በህብረተሰቡ ዘንድ የሚነሱ የልማት ክፍተት ለመሙላት መንግሥት እያደረገ ያለው ጥረት አበረታች መሆኑን በካፋ ዞን፣የኦዲዮ ካካ ምርጫ ክልል የኢፈዲሪ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት እና የክልል ምክር ቤት ተመራጮች ገልጸዋል። የምክር ቤቱ አባላት በአዲዮ ካካ ወረዳ እየተገነባ ያለውን የውሃ መሠረተ ልማት ስራዎች ተዘዋውሮ የጎበኙ ሲሆን በየደረጃው ያለው የመንግሥት መዋቅር በመቀናጀት ፕሮጀክቶቹን በአጭር ጊዜ በማጠናቀቅ ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ እያደረጉት…

Read More

24 ሚሊዮን ብር የፈጀው አዲሱ የጊንቦ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ማስፋፊያ ግንባታ ተመረቀ

በ2015 ዓመተ-ምህረት በጊንቦ ወረዳ አስተዳደር የበጀት ድጋፍና በማህበረሰቡ ተሳትፎ የተጀመረው ባለ 2 ወለል እና 12 መማሪያ ክፍሎች ያሉት የህንፃ ግንባታ በዛሬው ዕለት ተመርቋል፡፡ በምረቃ መርሃ ግብሩ ላይ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትመህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አልማው ዘውዴ፣ የቢሮው ምክትል ኃላፊ ዶክተር ደስታ ገነሜ፣ የካፋ ዞን የመንግስት ዋና…

Read More

በክልሉ ኪነ ጥበብ ለህዝቦች ትስስርና ለገዢ ትርክት ግንባታ ያለውን ትልቅ ሚና ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ

ኪነ-ጥበብና ስነ-ጥበብ ለህዝቦች አብሮነትና ለገጽታ ግንባታ በሚል መሪ ቃል በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጽያ ህዝቦች ክልል መንግስት ባህል ቱሪዝምና ስፓርት ቢሮ ለ2ኛ ጊዜ የተዘጋጀ ክልላዊ ውድድር በዳውሮ ዞን ታርጫ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል በመርሃ ግብሩ የተገኙት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ሃላፊ አቶ ፋንታሁን ብላቴ ባስተላለፉት መልዕክት ኪነ ጥበብ የሰው ልጅ የሚኖርበትን ዘመንና ጊዜን…

Read More

የክልሉ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ የ2017 ግማሽ በጀት አመት እቅድ አፈጻጸሙን እየገመገመ ነዉ ።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ የ2017 የ6 ወር እቅድ አፈጻጸምና የቀጣይ ቀሪ ወራት ዕቅድ ዙሪያ በቦንጋ ከተማ እየመከረ ይገኛል። በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ አንድነት አሸናፊ እንደተናገሩት በክልላችን የጸጥታ ስራዉ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መቶ ከቀዉስ ወደ አንጻራዊ ሰላም መሸጋገር ችለናል ብለዋል። ሰላምን ባረጋገጥንባቸዉ አካባቢዎችም ሰላምን…

Read More