Trendings

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ እና የኦሮምያ ክልል ርዕሰመስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ ጋር በአምቦ ወረዳ በነበራቸው ጉብኝት የኬኛ ቤቭሬጅ ፋብሪካን ተመልክተዋል። ፋብሪካው በመጪዎቹ ሶስት ሳምንታት ውስጥ ወደሥራ የሚገባ ሲሆን 3 ሚሊዮን ሄክቶሊትር የማምረት አቅምም አለው።

የአስተዳደር ሥራን ወደ ሕዝብ ለማቅረብ የቀበሌዎች መጠናከር ወሳኝ ነው። የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት በየአካባቢው ለሕዝብ ቅርብ የሆነ አስተዳደር ለመፍጠር (power devolution) ጥረት እያደረገ ነው። ከዚህ አንጻር በአምቦ ወረዳ የአንድ ቀበሌ እንቅስቃሴ በጉብኝት ወቅት ታይቷል። በዚህ ቀበሌን የማብቃት ተግባር በክልሉ 7342 ቀበሌዎች ተደራጅተዋል። 50,000 የሰው ኃይል ተመድቦላቸዋል። ከዚህ ቀደም በወረዳዎች ተማክለው የነበሩ ሞያዊና አስተዳደራዊ አገልግሎቶች በቀበሌ ደረጃ…

Read More

በክልሉ ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን በተለያዩ ኩነቶች ለማክበር ዝግጅት መጠናቀቁ ተገለጸ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ የዘንድሮ ማርች 8 ( አለምአቀፍ የሴቶች ቀን) በተለያዩ ዝግጅቶች እንደሚከበር አስታውቋል። የቢሮው ኃላፊ ወ/ሮ ገነት መኩሪያ እንደገለጹት፥ በሁሉም የክልሉ መዋቅሮች ቀድሞ በወረዳ መነሻ ዕቅድ መሠረት ቀኑ በተለያዩ ኩነቶች እና በመስክ ጉብኝት ይከበራል ብለዋል። በዓሉ በአለም አቀፍ ደረጃ ለ114ኛ በሀገራችን ደግሞ ለ49ኛ ጊዜ “ፈጣንና ቀጣይነት ያለው…

Read More

የብልፅግና ፓርቲ 2017 ዓ.ም በጀት ዓመት የ6 ወራት የስራ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ መካሄድ ጀምሯል።

በአጠቃላይ ሀገራዊ ፓለቲካ ሁኔታ፣ ጠንካራ ፓርቲ ግንባታ ለማሳካትና በፓርቲና በመንግሥት ቅንጅት የሚሰሩ የንቅናቄ አጀንዳዎችን የሚገመግመው መድረክ በብልፅግና ፓርቲ ዋና ፅ/ቤት ተጀምሯል። በመርሀ ግብሩ ላይ የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት ክቡር አቶ አደም ፋራህን ጨምሮ የብልፅግና ፓርቲ ዋና ፅ/ቤት የዘርፍ አመራሮች የክልል ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ኃላፊዎች እንዲሁም የክልል የአደረጃጀት እና የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። ለ3 ተከታታይ ቀናት ይካሄዳል…

Read More

ራስን በትጥቅ አቅም የመቻል የሪፎርም ስራ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል፦ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ

ራስን በትጥቅ አቅም የመቻል የሪፎርም ስራ ተጨባጭ ውጤቶች እየተገኙበት መሆኑን የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ገለጹ። ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ የሆሚቾ አሙኒሽን ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪን አስመልክቶ በሰጡት ማብራሪያ ከሀገር መከላከያ ሰራዊት ሪፎርም ዋነኛ የትኩረት ማዕከል አንዱ በትጥቅ ራስን መቻል እንደሆነ ገልጸዋል። ከዚህ ቀደም ኢትዮጵያ ጥይት እና ተተኳሽ ከውጭ ሀገራት ትገዛ እንደነበር ያወሱት…

Read More

ሪፖርታዥ

የህብረተሰብ ተሳትፎን በማላቅ በከተሞች የተጀመሩ ስራዎችን ከግብ ለማድረስ እየተሰራ እንደሆነ የከተማ አስተዳደሮች ገለጹ ከተሞች ለነዋሪዎች ለመኖሪያ ምቹና ፅዱ እንዲሆኑ የተለያዩ የልማትና መልካም አስተዳደር ተግባራት እየተከናወኑ ነው፤ ለውጥም እያመጡ መሆናቸውን የቴፒ፣ማጂ-ቱም እና ጪዳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባዎች ገልጸዋል። በመሆኑም የህብረተሰብ ተሳትፎን በማላቅና ቅንጅታዊ አሠራሩን ማጠናከር በከተሞች የተጀመሩ ስራዎችን ከግብ ለማድረስ ወሳኝ መሆኑን ከንቲባዎች ጠቁመዋል ። ቴፒ ፣…

Read More

የሚዛን አማን ከተማ የኮሪደር ልማት ሥራ ተጎበኘ

የክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ምክትል ሃላፊና የከተሞች መሬት አስተዳደር ዘርፍ ኃላፊ አቶ ጫናቸው ወንድሙ በሚዛን አማን የኮሪደር ልማትና ልዩ ልዩ የልማት ስራዎችን ተዘዋውረው ጎበኙ። በከተማዋ በመንግስትና ከፍተኛ የህዝብ ንቅናቄ ታክሎበት እየተገነባ ያለው የኮሪደር ልማት ስራ የመጀመሪያ ዙር በተያዘለት የጊዜ ገደብ እየሄደና በጥሩ አፈጻጸም ላይ የሚገኝ መሆኑንም በምልከታ ወቅት ተገልጿል። በመልሶ ማልማት ዘርፍ ከተማ አስተዳደሩ…

Read More

የምክር ቤት አባላት በልማትና መልካም አስተዳደር ስራዎች ዙሪያ የህዝብ መድረክ አካሄዱ

በካፋ ዞን፣የኦዲዮ ካካ ምርጫ ክልል የኢፈዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና የክልል ምክር ቤት ተመራጮች በልማትና መልካም አስተዳደር ስራዎች ዙሪያ የህዝብ መድረክ በካካ ከተማ አካሂደዋል። ከዚህ በፊት በህብረተሰቡ ሲነሳ የነበረውን የንጹህ መጠጥ ውሃ እና የመንገድ መሠረተ ልማት ችግሮች ለመፍታት መንግሥት የልማት አቅሞችን በማቀናጀት እያደረገ ያለው ርብርብ የሚደነቅ መሆኑን ያነሱት በኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባል ክብርት…

Read More

የግብርናውን ዘርፍ በቴክኖሎጂ በማስደገፍ ውጤታማ ማድረግ ያስፈልጋል:-አቶ ማስረሻ በላቸው

በጊምቦ ወረዳ ግብርና ደን አካባቢ ጥበቃና ህብረት ስራ ልማት ጽ/ቤት የግብርና ልማት ሰራተኞች የግምገማ ነክ ስልጠና መድረክ እየተካሄደ ይገኛል:: የግብርናውን ዘርፍ በቴክኖሎጂ በማስደገፍ ውጤታማ መሆን ያስፈልጋል ሲሉ የገለጹት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው የግብርና ባለሙያዎች በአርሶ አደሩ ማሳ የተጠናከረ የክትትልና ድጋፍ ስራ በመስራት ምርትና ምርታማነትን ማረጋገጥ…

Read More

የፌደራል እና የክልል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ከሰሜን ቤንች ወረዳ ህዝብ ጋር በልማትና በመልካም አስተዳደር ችግሮች ዙሪያ ተወያዩ።

በሰሜን ቤንች ወረዳ ከህዝብ የተወከሉ የፌዴራልና የክልል ምክር ቤት አባላት ከማህበረሰብ ክፍሎች የተወጣጡ የህዝብ ተወካዮች ጋር በልማትና በመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ አካሂዷል። በህዝቡ ዘንድ አለአግባብ (ህገወጥ)ጥሎሽ ወጣቶችን አላሰፈላጊ ድርጊት ውስጥ እንዲገቡ ያደረጋል ስለዚህ መፈትሔ እንዲያገኝ በፌደራል እና በክልል ደረጃ ህጋዊ ግራውንድ እንዲይዝ ቢደረግ የሚሉና መሰል የመልካም አሰተዳደር ችግሮች በሰፊው ተነስተዋል። በተጨማሪ የኑሮ…

Read More

በዞኑ ያለውን ፀጋ በአግባቡ በመጠቀም የህዝቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን መመለስ እንደሚገባ ተገለፀ

የፌደራል እና የክልል ተመራጮች ለዞኑ አስፈፃሚ አካላትና ለሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት የመስክ ምልከታና የህዝብ ውይይት ግብረ መልስ በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ ሰጥተዋል። በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ የተከበሩ አቶ አዝመራ አንደሞ እንደገለፁት ሁሉ አቀፍ በፌደራልና በክልል መንግስት እየተገነቡ ያሉ ፕሮጀክቶች የመንገድ፣ የውሃ እና የመብራት ስራ አፈጻጸም ተስፋ ሰጪ መሆኑን ገልፀው ተጠናክሮ…

Read More