ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በጋሞ ዞን በደረሰው አደጋ ለተጎዱ ወገኖች የተሰማቸውን ኀዘን ገለጹ
የሩሲያ ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን በደረሰው የመሬት መንሸራተትና የጎርፍ አደጋ ሕይወታቸውን ላጡ እና ለተጎጉ ዜጎች የተሰማቸውን ጥልቅ ኀዘን ገለጹ። ፕሬዚዳንቱ ለኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታየ አጽቀ ሥላሴ እና ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በላኩት መልዕክት፣ በአደጋው ሳቢያ ለተጎዱ ወገኖች ያላቸውን አጋርነት ገልጸዋል። በመሬት መንሸራተቱ ሕይወታቸውን ላጡ ወገኖች ቤተሰቦችና ወዳጅ ዘመዶች መጽናናትን የተመኙት ፕሬዚዳንት…
