Trendings

በክልሉ የሚሰበሰበው ገቢ ውጤታማ ለማድረግ በቴክኖሎጂ የተደገፈ የአገልግሎት አሰጣጥ ስርዓትን ማጠናከር ይገባል ስሉ ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ ገለጹ

የክልሉ ገቢዎች ቢሮ የ2017 በጀት ዓመት የ10 ወራት የገቢ አሰባሰብ የምክክር መድረክ ከባለድርሻ አካላት ጋር አድርጓል ። በምክክር መድረኩ የተገኙት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ ክልሉ የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ ገቢን በመሰብሰብ ህብረተሰቡ የሚጠይቀውን የልማት ጥያቄ መመለስ ይገባል ብለዋል። በክልሉ የግብር ስወራንና የገቢ ማጭበርበርን ለመከላከል በቴክኖሎጂ የተደገፈ የአገልግሎት አሰጣጥ ስርዓትን…

Read More

ብልጽግና ፓርቲ ባለፉት የለውጥ አመታት ውስጥ የተዘነጉ አካባቢዎች ፍትሐዊ ተሳትፎና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ያረጋገጠ ተግባራትን አከናዉኗልናል። ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)

ምዕራብ ኦሞ ዞን ጀሙ ከተማ የብልፅግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳና ህዝባዊ ድጋፍ ሰልፍ ተካሄደ። ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በሰልፉ ባስተላለፉት መልዕክት ባለፉት የለዉጥ ዓመታት የብልፅግና ፓርቲ በቀደሙት ስርአት የተረሱ አካባቢዎችን በማስታወስ እኩል የልማትና መልካም አስተዳደር ተሳታፊ እና ተጠቃሚ በማድረግ ከፍተኛ ለውጥ ካስመዘገበባቸው አካባቢዎች የምዕራብ ኦሞ ዞን አንዱ መሆኑን ገልጸዋል። ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ…

Read More

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ሴክቶሪያል ጉባዔ ተጠናቀቀ::

ቢሮው በሚዛን አማን ከተማ ሲያካሂድ የቆዬውን የ6 ወራት አፈፃፀምና የቀጣይ አቅጣጫዎች እንዲሁም ለተለያዩ የፋይናንስ ህግ ማዕቀፎች ዝግጅት ግብዓት ማሰባሰብ ላይ ያተኮረ ጉባዔ አጠናቋል። ጉባዔው በቆይታው የ2016 በጀት ዓመት የ6 ወራት የአፈፃፀም ሪፓርት በስፋት የተወያየበት ሲሆን በሪፖርቱ በተለይም ሲንከባለል የመጣ የግብዓትና የጡረታ ዕዳ ለማስመለስ የተከናወኑ ተግባራት አበረታች ቢሆኑም ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተመላክቷል። የክልሉ ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት…

Read More

በክልሉ የሕዝቡን ችግር በማድመጥ ምላሽ የመስጠቱ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ገለጹ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልሰ በብልፅግና ፓርቲ ለሕዝብ ተወካዮችና ለክልል ምክር ቤት የቀረቡ ዕጩ ተወዳዳሪዎች ጋር በቀጣይ ተልዕኮዎች ዙሪያ በቦንጋ ከተማ የተካሄደው የምክክር መድረክ ተጠናቋል። በምክክር መድረኩ ባለፉት አምስት ዓመታት የተከናወኑ ተግባራት አፈጻጸም በመገምገምና በቀጣዩ ጊዜያት መፈጸም በሚገባቸው ተልዕኮዎች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል። የምክክሩ ተሳታፊ የሁለቱ ክልል ምክር ቤት የሕዝብ ተወካዮች ፤ የክልሉ ሕዝብ የዘመናት በክልል…

Read More

ጠቅላይ ሚኒስር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ስለባሕር ዳር ልምድ ያነሷቸው ነጥቦች

ዛሬ የባሕርዳርን ከተማ የኮሪደር ልማት እንቅስቃሴ ተመልክቻለሁ። ተፈጥሮ እና የሰው ጥበብ ተዋሕደው ባሕርዳርን ይበልጥ ውበቷን እያወጡት ነው። ከተማዋን የንግድና የቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ አመራሩ ከሚያደርገው ጥረት የምንማራቸው ብዙ ነገሮች አሉ። 1. ባሕር ዳር በፈተና ውስጥ የመጽናት ምሳሌ ናት፤ ባለፉት ዓመታት የነበረው ፈተና እያለፈ ነው። ባሕር ዳር በፈተናው ውስጥ ሥራዋን አላቋረጠችም። እንዲያውም ለፈተና የተወረወረውን ድንጋይ ለግንባታ ተጠቅማበታለች።…

Read More

በክልሉ የተገኘዉን ሠላም ዘላቂነት የማጽናት ትልም!

ሠላም ለሁሉም ነገር መሠረት ነው፡፡ ወጥቶ ለመግባት፣አርሶ ለመብላት፣ወልዶ ለመሳም፣ተምሮ ለመጨረስ፣ተኝቶ ለመታከም በአጠቃላይ ለሰዉ ልጆች ብቻ ሳይሆን ህይወት ላለዉ ነገር ሁሉ ሰላም ወሳኝ መሣሪያ ነዉ።ሠላም በእጃችን ያለ ትልቅ ዉድ ሃብት ነዉ።የቀዬዉ ሰዉ ጧት ማልዶ ለጉዳዩ ሲወጣ“አቤቱ በሠላም አዉለኝ”የሚለዉ የሠላምን ዋጋ ጠንቅቆ ስለሚረዳ ነዉ። በሠላም ወጥቶ መመለስ ምኑን ያህል ጣፋጭ እንደሆነ ስለሚረዳ ነዉ።ሠላም የትም ያለ፣ከሌላ ቦታ የሚገኝ…

Read More

ሰሜን ዕዝ ላይ ጥቃት የተፈፀመበት 4ኛ ዓመት ታስቦ ዋለ

በሀገር መከላከያ ሰራዊት ሰሜን ዕዝ ላይ ጥቃት የተፈፀመበት 4ኛ ዓመት በመከላከያ ጠቅላይ መምሪያ ታስቦ ዋለ። “እንዳይደገም ሁሌም እንዘክረዋለን” በሚል መሪ ሀሳብ በተዘከረው በዚህ ሥነ-ሥርዓት ላይ ሰሜን ዕዝ ከሁለት አሥርት ዓመታት በላይ እውቀቱን፣ ገንዘቡን፣ ጉልበቱንና ሕይወቱን ሳይሰስት ስለመስጠቱ ተነስቷል። በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የመከላከያ ሠራዊት ሥነ-ልቦና ግንባታ ዋና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ሜጀር ጄኔራል እንዳልካቸው ወልደኪዳን፤ ለሕዝብና ለሀገር ዋጋ…

Read More

ኢትዮጵያ ለ400 ሺህ ኤርትራውያን ስደተኞች ቤት ነች፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ኢትዮጵያ አሁን ላይ ለ400 ሺህ ኤርትራውያን ስደተኞች መኖሪያ እና መጠለያ ቤት እንደሆነች ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ሀገራችን ኤርትራውያኑን ጨምሮ ከተለያዩ ሀገራት የተሰደዱ በአጠቃላይ ለ1.3 ሚሊዮን ስደተኞች ቤት መሆን የቻለች ሀገር ናት ብለዋል። ሀገራችንን በወጉ መገንባት ከቻልን ለዜጎቻችን ብቻ ሳይሆን ለሌሎችም አርአያ መሆን የሚችል እና የሚተርፍ ውጤት ማምጣት እንደምንችልም አስገንዝበዋል። ኢትዮጵያ ከአፍሪካ በሕዝብ ቁጥር…

Read More

44ኛው የአፍሪካ ሕብረት አስፈጻሚዎች መደበኛ ስብስባ ተጠናቀቀ::

44ኛው የአፍሪካ ሕብረት አስፈጻሚዎች ምክር ቤት መደበኛ ስብስባ ዛሬ ማለዳ ተጠናቋል። ስብሰባው “ለ21ኛው ክፍለ ዘመን የሚመጥን አፍሪካዊ ማስተማር፤ የማይበገሩ የትምህርት ስርዓቶች በመገንባት በአፍሪካ ሁሉን አቀፍ፣ የሕይወት ዘመን፣ ጥራትና አግባብነት ያለው የትምህርት ተደራሽነትን ማስፋት“ በሚል የአፍሪካ ሕብረት ባዘጋጀው የ2024 መሪ ሀሳብ ሲካሄድ ቆይቷል። ምክር ቤቱ ከጥር 6 እስከ 17 ቀን 2016 ዓ.ም 47ኛው የአፍሪካ ሕብረት ቋሚ…

Read More

ርዕሰ መስተዳድር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በተገኙበት በኮንታ ዞን አመያ ከተማ ታላቅ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሄደ ይገኛል።

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በኮንታ ዞን አመያ ከተማ የብልፅግና ፓርቲን የሚደግፍና ህዝባዊ መሰረቱን የሚያሳይ ታላቅና ደማቅ ሰልፍ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የአመያ ከተማና የአካባቢው ነዋሪዎች ከጠዋቱ ጀምሮ አደባባዮችን በፓርቲው አርማዎች፣ ባነሮችና በተለያዩ መፈክሮች በማጌጥ፣ ለብልፅግና ፓርቲ ያላቸውን የማይናወጥ ድጋፍና አጋርነት በታላቅ የደስታ ስሜት እየገለጹ ይገኛል። ህዝባዊ ሰልፋ የብልፅግና ፓርቲ ወደ ስልጣን ከመጣበት ጊዜ ጀምሮ በሀገሪቱና…

Read More