የህብረተሰብ ተወካዮች በአጀንዳ ሃሳቦች ላይ እያደረጉት ያለው ውይይት እንደቀጠለ ነው
ሁለተኛ ቀኑን ያስቆጠረውና የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአዲስ አበባ ከተማ እያስተባበረ የሚኘው የምክክር ምዕራፍ ዛሬም ቀጥሏል፡፡ ከትናንት ግንቦት 21 ቀን 2016 ከሰዓት በኋላ ጀምሮ በነበረው መርሃ-ግብር ተሳታፊዎች በየህብረተሰብ ክፍላቸው በቡድን በመሆን ከወከሉት ማህበረሰብ በአደራ ያመጧቸው የአጀንዳ ሀሳቦች ላይ ውይይት እያደረጉ ይገኛሉ፡፡ በሂደቱ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች የኛ የሚሉትን እና የተስማሙባቸውን የአጀንዳ ሀሳቦች በማጠናቀር ለኮሚሽኑ በቃለ-ጉባኤ ተፈራርመው…
