በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የአስተዳደር ብልጽግና ህብረት የ2017 ዓ/ም ዕቅድ አፈጻጸምና የ2018 ዓ/ም ዕቅድ ዙሪያ ከአባላት ጋር እየገመገመ ነው።
በበጀት ዓመቱ ታቅደው በብልጽግና ቤተሰብ ደረጃ የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትን የተመለከተ ሪፖርት ህብረቱ ሰብሳቢ አቶ ሳምሶን መለሰ አቅርበዋል ። የህብረቱ ሰብሳቢ ባቀረቡት ሪፖርት የብልጽግና ቤተሰብ በበጀት ዓመቱ ዕቅዳቸውን ውጤታማ እንዲያደርጉ ተገቢው የድጋፍና ክትትል ስራዎች መሰራታቸውን አብራርተዋል ። ከክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የሚወርዱ ሀገር አቀፍና ክልል አቀፍ ይዘት ያሏቸውን ተልዕኮ ለመፈጸም እንዲያስችል የአባላት አቅም ግንባታ…
