ጥራት ያለውን ቡና በማዘጋጀት ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ ተገለጸ።
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ከፍተኛ መጠን ያለውን ቡና ለማዕከላዊ ገበያ በማቅረብ ከግምባር ቀደሞቹ ተርታ የሚመደብ ቡና አምራች አከባቢ ነው። በክልሉ ቤንች ሸኮ ዞን፣ ደቡብ ቤንች ወረዳ ቡና በስፋት እንደሚለማ የገለጹት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ተሾመ ኪያስካ በዚህም የአምራች አርሶአደሮች ገቢ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱን ተናግረዋል። የቡና ጥራት ለማስጠበቅ ተግባራዊ የኾነው የቡና ፓኬጅ ማሻሻያ…
