በመንግሥት ከፍተኛ ድጎማ የሚቀርበውን ነዳጅ ከተተመነለት የዋጋ መጠንና የግብይት ሰንሰለት ውጪ በሚሸጡ ሕገወጦች ላይ የተጠናከረ እርምጃ መውስድ ተጀምሯል
በመንግሥት ከፍተኛ ድጎማ የሚቀርበውን ነዳጅ ከተተመነለት የዋጋ መጠንና የግብይት ሰንሰለት ውጪ በሚሸጡ ሕገወጦች ላይ የተጠናከረ እርምጃ መውስድ መጀመሩን የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ አስታወቁ። የገንዘብ ሚኒስትሩ አሕመድ ሽዴ በነዳጅ አቅርቦት ዙሪያ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ፤ መንግሥት በዓለም ተለዋዋጭ የገበያ ሁኔታ ውስጥ የህዝብን ጫና ለመቀነስ በቢሊየን የሚቆጠር ዶላር ድጎማ እያደረገ ነው ብለዋል። በዚህም መንግሥት ነዳጅን ለኅብረተሰቡ ተደራሽ…
