ታላቁን የጥምቀት በዓልን ሲናከብር በመከባበርና በመተባበር ሊሆን ይገባል።ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት በየዓመቱ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሚከበሩ የአደባባይ በዓላት አንዱ የሆነው የከተራና የጥምቀት በዓል እንኳን አደረሳችሁ ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል። ሀገራችን ኢትዮጵያ የቆየ ባህላዊና ሃይማኖታዊ እሴቶች ያሏት ታሪካዊት ሀገር ነች ሲሉ ርዕሰ መስተዳድሩ ተናግረዋል ። የከተራና የጥምቀት በዓላት የሰላም፣ የአብሮነት፣ የመተሳሰብና የአንድነት…
