በሀገሪቱ ችግር እየፈጠሩ የሚገኙ አካላት ላይ ህግ የማስከበር ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
መንግስት በሀገሪቱ ችግር እየፈጠሩ የሚገኙ አካላት ላይ ህግ ማስከበሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እያካሄደ በሚገኘው 14ኛ መደበኛ ስብሰባ ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። በማብራሪያቸውም ኢትዮጵያ ውስጥ እየተነዛ ያለው የተዛባ መረጃና ፕሮፓጋንዳ አፍራሽ ነገሮችን እያባባሰ መሆኑን ተናግረዋል። በአስተሳሰብ ረገድ ክላሽ ይዞ ዘራፍ የሚል የአርበኝነት…
