Trendings

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ ካነሷቸው ዋና ዋና ጉዳዮች መካከል፡-

👉 ባለፉት ሦስት ወራት 180 ቢሊየን ብር ገቢ ሰብስበናል፡፡ ባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት 109 ቢሊየን ብር ነበር የተሰበሰበው፡፡ የልዩነቱ ስፋት ለውጥ እንዳለ እና መንገዳችን ትክክል እንደሆነ አመላክች ነው፡፡ 👉 በፌደራል መንግሥት 900 ቢሊየን ብር በክልሎች ደግሞ 600 ቢሊየን ብር ገቢ መሠብሰብ ከተቻለ በአጠቃላይ 1 ነጥብ 5 ትሪሊየን ገደማ እንሰበስባለን ማት ነው፡፡ ይህም በቂ ባይሆንም ትልቅ…

Read More

በየነ ጴጥሮስ(ፕ/ር) የሰሩት ስራ የሚያኮራ ነው – ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር)

በየነ ጴጥሮስ (ፕ/ር) በህይወት ሳሉ የሰሩት ስራ የሚያኮራ በመሆኑ ትውልድ ከእርሳቸው ህይወት ሊማር ይገባል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። የበየነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) የአስከሬን ሽኝት በሚሊኒየም አዳራሽ እየተካሄደ ነው። በሽኝት መርሐ ግብሩ የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ባስተላለፉት መልዕክት፤ በየነ ጴጥሮስ (ፕ/ር) በህይወት ዘመናቸው የሰሩት ስራ የሚያኮራ በመሆኑ ትውልድ ከእርሳቸው ህይወት ሊማር እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡…

Read More

በሚዛን አማን ከተማ ለብልጽግና ፓርቲ ደጋፊዎች ያሳተፈ ታላቅ የድጋፍ ሰልፍ ተካሄደ

ሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር የብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ “ብልጽግና ፓርቲን ይምረጡ” በሚል መሪ ቃል በከተማዋ ደማቅ የድጋፍ ሰልፍ አካሄደ። በተሽከርካሪዎች የታገዘው በዚህ ሰልፍ ላይ የከተማዋ ነዋሪዎች፣ በርካታ ወጣቶችና የአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል። በድጋፍ ሰልፉ ላይ የተሳተፉት የሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ኢንጂነር ሰለሞን ለዊ እና የከተማው ብልጽግና ፓርቲ የፖለቲካና የሕዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊና ረዳት ተጠሪ…

Read More

“ባለፉት ሶስት ወራት ከ20 የማያንሱ ዓለም አቀፍ ኮንፈረንሶች በኢትዮጵያ ተካሂደዋል”

ባለፉት ሶስት ወራት ከ20 የማያንሱ ዓለም አቀፍ ኮንፈረንሶች ተካሂደዋል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስተርር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ባለፈው ዓመት ዓመቱን ሙሉ 20 ዓለም አቀፍ ኮንፈረሶችን አላካሄድንም፤ ዘንድሮ በሶስት ወር ብቻ 20 የሚደርሱ ዓለም አቀፍ ኮንፈረንሶችን አካሂደናል ብለዋል፡፡ በቀጣይም በርካታ ዓለም ዓቀፍ ኮንፈረንሶች በኢትዮጵያ ይካሔዳሉ ሲሉ አመላክተዋል፡፡ የኮሪደር ልማት እና በኢትዮጵያ የተፈጠረው አውድ ዓለም አቀፍ ጎብኚዎችን ኮንፈረንሶችን…

Read More

2 ሺህ የሚሆኑ የቅድመ ወሊድና የወሊድ አገልግሎት መስጫ ማዕከላትን በኢትዮጵያ ለመገንባት የሚያስችል የሶስትዮሽ የመግባቢያ ስምምነት ተፈረመ፡፡

ስምምነቱን ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ እና በሩሲያ የፓን አፍሪካ የመንግስትና የግል አጋርነት የልማት ማዕከል ናቸው የተፈራረሙት፡፡ ስምምነቱ የእናቶችንና የጨቅላ ህፃናትን ህይወት ለማሻሻል የሚረዳ በአይነቱ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ‘ሚድ ዋይፈሪ’ ማዕከል እንደሚሆን ተጠቅሷል፡፡ የሩሲያው የፓን አፍሪካ የመንግስትና የግል አጋርነት የልማት ማዕከል ወደ ሀገር እንዲመጣ የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ላበረከተው አስተዋፅኦ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ…

Read More

ዞናዊ ነበራዊ ሁኔታን መሠረት ያደረገ አጠቃላይ የዞን አመራርና ወረዳ አስተባባሪ ኮሚቴዎች ጋር ውይይት እየተካሄደ ይገኛል።

የካፋ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ዞናዊ ነባራዊ ሁኔታን መሠረት ያደረገ አጠቃላይ የዞን አመራርና የወረዳ እና ከተማ አስዳደር አስተባባሪ ኮሚቴዎች ጋር ውይይት በቦንጋ ከተማ እያካሄደ ይገኛል። በውይይቱ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የካፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳሻው ከበደ፥ የመድረኩ ዓላማ ቀደም ሲል በተሰጡ የአመራር መድረኮች የተገኙ አቅሞችን በማቀናጀትና በአመራር መካከል የተግባር አንድነትን በመፍጠር የህዝብ የልማት አቅሞችን…

Read More

በዳውሮ ዞን የመንግሥትና የፓርቲ ሥራዎች እንዲሁም የምርጫ ሂደት ያለበት ደረጃ መገምገሙ ተገለጸ

በዳውሮ ዞን የተከናወኑ የመንግሥትና የፓርቲ ሥራዎች እንዲሁም የምርጫ ዝግጅት ያለበት ደረጃ በከፍተኛ አመራሮችና በየደረጃው በሚገኙ የሥራ ኃላፊዎች በዝርዝር ተገምግሟል። በግምገማ መድረኩ ላይ የተገኙት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል መንግሥት ሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ አንድነት አሸናፊ በዞኑ የተጀመሩ የመንግስት እና የፓርቲ ሥራዎች ስኬታማ መሆን የሚያስችል ስራ መሰራት እንዳለበትም ገልጸዋል። የሕዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የመንግሥትና…

Read More

የአፈር ማዳበሪያ ስርጭት እና ዕዳ አመላለስ አስተዳደር ሥርዓትን የማዘመኑ እንቅስቃሴ ተጠናክሮ ይቀጥላል ፦ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ ከኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ጋር በመቀናጀት የኤሌክትሮኒክስ ቫውቸር (E-VOUCHER) ሥርዓት የግብርና ግብዓት ሽያጭ ይፋዊ ሥራ ማስጀመሪያ በቦንጋ ከተማ እያካሄደ ይገኛል። በማስጀመሪያው የተገኙት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) እንደተናገሩት እንደሀገር የዲጂታል ኢኮኖሚን ለማሳለጥ በተለያዩ ዘርፎች በተጀመሩ ሥራዎች ተጨባጭ ውጤቶች እየተመዘገቡ ናቸው። ይህን ሀገራዊ የዲጂታል ኢኮኖሚ ሥርዓትን የማሳለጡ…

Read More

በጋምቤላ ክልል ከወዳደቁ ፕላስቲኮች ነዳጅ ማምረት የቻለው ግለሰብ

በጋምቤላ ክልል አኙዋ ዞን ጎግ ወረዳ የሚኖረው አቶ ኡጁሉ ኡሞድ የወዳደቁ ፕላስቲክ እቃዎችን እና ፌስታሎችን በመሰብሰብ የቤንዚን እና የናፍታ ነዳጅ ማምረት ችሏል። የወዳደቁ ፕላስቲኮችን እና ፌስታሎችን ሲሰበስብ ሰዎች እንደ እብድ ይቆጥሩት እንደነበር የገለጸው አቶ ኡጁሉ፤ የወዳደቁ የፕላስቲክ እቃዎችና ፌስታሎችን በመሰብሰብ የቤንዚንና ናፍታ ነዳጅ በመስራት ውጤታማ መሆኑን ገልጿል። በአሁኑ ሰዓት የነዳጅ ምርቱ በጀነሬተር እና በሞተር ሳይክል…

Read More

በተሻሻለው የወንጀል ቅጣት አወሳሰን መመሪያ ቁጥር 03/2017 ላይ እና በዳኞች ሥነ- ምግባር ዙርያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በዳውሮ ዞን ከፍተኛ፣ የወረዳ እና ከተማ አስተዳደር ፍርድ ቤቶች ለተወጣጡ ዳኞች በተሻሻለው የወንጀል ቅጣት አወሳሰን መመሪያ ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና በታርጫ ከተማ እየሰጠ ይገኛል። መድረኩን በንግግር የከፈቱት የዳውሮ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕረዚዳንት አቶ አሮታ አልባዞ እንደገለፁት የስልጠናው ዓላማ የዳኝነት አካሉን ግልፅነት እና ተጠያቂነት ባረጋገጠ መልኩ ውጤታማ እና…

Read More