Trendings

በዳዉሮ ዞን ታርጫ ጠቅላላ ሆስፒታል በማኅጸን ውልቃት የሕክምና ዘርፍ እየተሰጠ የሚገኘው አገልግሎት በተሻለ ሁኔታ እንዲሰጥ ለማድረግ የተቀናጀ ርብርብ እንደሚጠይቅ ተገለጸ።

አገልግሎቱን የበለጠ ተደራሽ ለማድረግ የባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ ተግባሩ እየተመራ እንዳለም የሚመለከታቸው የሥራ ኃላፊዎች ተናግረዋል። በዳዉሮ ዞን የታርጫ ጠቅላላ ሆስፒታል በተለያዩ የሕክምና ዓይነቶች በሰለጠኑ ባለሙያዎች አገልግሎቱን ተደራሽ እያደረገ እንደሚገኝ ከሆስፒታሉ ያገኘነው መረጃ ያሳያል። በተለይም በማህጸንና ጽንስ፣ በሕጻናት፣ በአጥንትና ድንገተኛ አደጋዎች፣ በአጠቃላይ ቀዶ ጥገናና በውስጥ ደዌ በሽታዎች በስፔሻሊት ደረጃ የሕክምና አገልግሎቱ እየተሰጠ ይገኛል። ከእነዚህ አንዱ በሆነው በማኅጸንና…

Read More

የሴቶችን ሁለንተናዊ ተሳታፊነትና ተጠቃሚነት ሚና እንዲጎለበት የሴቶች ኮከስ አደረጃጀት ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ ተገለፀ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የሴት ተመራጭ ኮከስ አባላት ከክልሉ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ጋር በመተባበር በኮከሱ ማስፈፀሚያ መመሪያ እና እስከአሁን አፈፃፀም ላይ በቦንጋ ከተማ የምክክር መድረክ አካሂዷል። በመድረኩ የተገኙ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ምክትል አፈ ጉባኤ ክብርት ወ/ሮ ፀሀይ ደርጫ እንደ ክልል ምክር ቤት የሴቶች ኮከስ ተግባር ደንብ ወጥቶለት ወደ…

Read More

በክልሉ እየተከናወኑ ያሉ ሁሉ አቀፍ የወባ መከላከልና መቆጣጠር እንዲሁም መደበኛ የጤና ተግባራት ስራዎች ተጠናክሮ ልቀጥል እንደሚገባ ተገለፀ

የጤና ሚኒስቴር ሱፐርቪዥን ቡድን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በዳውሮ፣ ኮንታና ካፋ ዞን ገወታ ወረዳ ያካሄደውን ሁለተኛ ዙር የድጋፍና ክትትል ስራዎችን አጠናቋል። የሱፐርቪዥን ቡድኑ በክልሉ እየተከናወኑ ያሉ ሁሉ አቀፍ የወባ መከላከልና መቆጣጠር እንዲሁም መደበኛ የጤና ተግባራት ስራዎች ተጠናክሮ ልቀጥል እንደሚገባ ገልፀዋል። በክልሉ ያለውን መሠረታዊ የጤና አገለግሎት አሰጣጥ ደረጃ ማረጋገጥና በጋራ በሚከናወኑ ተግባራት ዙሪያ መግባባት መፍጠር…

Read More

የክልሉ የሥነ-ምግባርና ፀረ – ሙስና ኮሚሽን በሃብት ማሳወቅና ምዝገባ ሂደት ላይ ለካፋ ዞን ማዕከል የመንግስት ሰራተኞች ስልጠና ሰጠ ።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የስነ-ምግባርና ፀረ – ሙስና ኮሚሽን ከአስር ቀን በኋላ ተግባራዊ የሚደረገውን የሃብት ማሳወቅና ምዝገባ ሂደት አስመልክቶ ከካፋ ዞን ማዕከል ለተወጣጡ መንግስት ሰራተኞች በቦንጋ ከተማ የግንዛቤ ስልጠና ሰጥቷል። በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር አቶ ዳግም ዳንኤል ሃብት ማሳወቅና ማስመዝገብ በመንግስት ተቋማት፡ በመንግስት የልማት ድርጅቶችና በህዝባዊ ድርጅቶች መካከል መልካም ስነ-ምግባርና እሴተቶች…

Read More

የትምህርት ጥራትን በማረጋገጥ ብቁና ተወዳዳሪ ዜጋ ለመፍጠር በሚደረገዉ ርብርብ የግል ኮሌጆች ሚናቸዉን በግባቡ ሊወጡ ይገባል፦አቶ ተስፋዬ እንዳሻዉ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ስራና ክህሎት ቢሮ በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ዘርፍ ከግል ኮሌጆች እና ከባለድርሻ አካላት ጋር በቦንጋ ከተማ የምክክር መድረክ አካሄደ። የክልሉ ስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ተስፋዬ እንዳሻዉ በመክፈቻ ንግግራቸዉ ብቁ የሆኑ ዜጎችን ለመፍጠር የግል ኮሌጆች ሚናቸዉ የጓላ መሆኑን ገልጸው የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በሚደረገዉ ርብርብ የግል ኮሌጆች ሚናቸዉን በአግባቡ መወጣት አለባቸዉ…

Read More

አዲሱን ሪፎርም መሰረት ባደረገ መልኩ በአንድ ማዕከል ዉስጥ ለህብረተሰቡ አገልግሎት መስጠት ወሳኝ መሆኑ ተገለፀ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ሥራና ክህሎት ቢሮ በአዲሱ ሪፎርም ዕሳቤዎችና በአንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ ለዘርፉ አመራሮችና ባለሙያዎች በቦንጋ ከተማ ስልጠና ሰጠ። የክልሉ ስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ተስፋዬ እንዳሻዉ በመክፍቻ ንግግራቸው እንደገለጹት አዲሱን ሪፎርም መሰረት ባደረገ መልኩ በአንድ ማዕከል ለህብረተሰቡ አገልግሎት በመስጠት እና የአሰራር ስርዓቱን በማሻሻል ከወቅቱ እሳቤ ጋር በማስተሳሰር የተሻለ ዉጤት ማስመዝገብ…

Read More

የአረንጓዴ ዐሻራና የተጎሳቆለ መሬት ማገገሚያ ልዩ ፈንድ ማቋቋሚያና አሥተዳደር አዋጅ ጸደቀ

ኢትዮጵያ በደን ዘርፍ ከልማት አጋሮች የምታገኘውን ድጋፍና ጥቅም ለማሳደግ የሚያስችል የአረንጓዴ ዐሻራና የተጎሳቆለ መሬት ማገገሚያ ልዩ ፈንድ ማቋቋሚያና አሥተዳደር አዋጅ ፀደቀ፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 12ኛ መደበኛ ስብሰባ÷ የአረንጓዴ ዐሻራ እና የተጎሳቆለ መሬት ማገገሚያ ልዩ ፈንድ ማቋቋሚያ እና አሥተዳደር አዋጅን በሙሉ ድምጽ አፅድቋል፡፡ የምክር ቤቱ አባላት አዋጁን አስመልክተው በሰጡት አስተያየት÷ ዘላቂ ፈንድ ከማቋቋም…

Read More

በጎልማሶችና መደበኛ ያልሆነ ትምህርት ላይ የተጀመሩ ስራዎች በተቀናጀ መልኩ ተጠናክሮ እንደሚቀጥሉ የክልሉ ትምህርት ቢሮ ገለጸ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ትምህርት ቢሮ ከዩኒሴፍ ጋር በመተባበር በጎልማሶችና መደበኛ ባልሆነ ትምህርት አሰራርና አደረጃጀት ዙሪያ የአቅም ግንባታ ስልጠና በቦንጋ ከተማ እየሰጠ ይገኛል። ስልጠናው በተፋጠነ ትምህርት ጋይድ ላይን፣ የጎልማሶች ክህሎት ማበልጸጊያና የመሠረታዊ ትምህርት ማመቻቸት ሥነ ዘዴ ትምህርት ላይ ያተኮረ ነው። የክልሉ ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊና የመማር ማስተማር ዘርፍ ኃላፊ ዶ/ር ደሰታ ገነሜ በወቅቱ እንደገለጹት፤በክልሉ…

Read More

ጤናማና አምራች ዜጋ ለመፍጠር በምግብና ስርዓተ ምግብ አተገባበር ላይ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ይገኛል ።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ጤና ቢሮ ከዩኒሴፍ ጋር በመተባበር በምግብና ስርዓተ ምግብ ፕሮግራም ማስጀመሪያ ዙሪያ ለባለድርሻ አካላት የግንዛቤ መፍጠሪያ መድረክ ተካሂዷል። በመድረኩ የተገኙ የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ተማም በክልሉ ጤናማና አምራች ዜጋ ለመፍጠር በምግብና ስርዓተ ምግብ አተገባበር ላይ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ይገኛል። በክልሉ የነፍሰ ጡርና አጥቢ እናቶች እንዲሁም ከአምስት አመትና ከሁለት…

Read More

የኤች አይቪ/ኤዲስን ለመከላከል ዘመናዊና ሐይማኖታዊ ፈውስን በጥምረት መጠቀም አስፈላጊ መሆኑ ተገለፀ

የኢትዮጵያ የሐይማኖት ተቋማት ጉባኤ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በፀረ -ኤች አይቪ/ኤዲስ መድኃኒት ቁርጠኝነትና ታካሚዎች ህክምናቸውን በመውሰድ በቀጣይነት የማቆየት ላይ የሚመክር ክልላዊ የአድቮኬሲ መድረክ በሚዛን አማን ከተማ አካሂዷል። በመድረኩ “መመርመር ራስን ለማወቅ፤ ቅዱሳት መጸሕፍት የፀረ – ዠኤች አይቪ/መድኃኒት መውሰድን ይፈቅዳሉ” በሚል መሪ ቃል የተካሄደ ሲሆን በመድረኩም ቫይረሱ በደማቸው ያላባቸው ወገኖች የጸረ-ኤች አይቪ/ኤድስ መድኃኒትን በሐኪም ትዕዛዝ…

Read More