Trendings

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ጤና ቢሮ የሰቆጣ ቃል ኪዳን ተግባሪ ወረዳዎች ጋር የ2016 ዓ/ም በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማና የ2017 ዓ/ም እቅድ ዙሪያ ምክክር አድርጓል ።

በሰቆጣ ቃልኪዳን የህጻናት መቀንጨር ከምግብ ስርአት ጋር ተያይዞ በርከት ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ የክልሉ መንግስት ከ11 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት መመደቡም ታውቋል ፡፡ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ጤና ቢሮ የሰቆጣ ቃል ኪዳን ተግባሪ ወረዳዎች ጋር የ2016 ዓ/ም በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማና የ2017 ዓ/ም እቅድ ዙሪያ በሚዛን አማን ከተማ ምክክር አድርጓል ። በክልሉ ጤና ቢሮ…

Read More

ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል እና ከጋምቤላ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጆች ለተውጣጡ ዲኖች ፣ አሰልጣኞችና ለሌሎችም ባለድርሻ አካላት በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ቴፒ ግቢ ስልጠና መስጠት ተጀመረ።

የሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አበበ ማሞ ለሰልጣኞች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ባስተላለፉበት ወቅት ዞኑ በተፈጥሮ ሀብቱ የበለፀገ በተለይም በተፈጥሮ ደን፣ በቱሪስት መስህቦች፣ ቡናና ቅመማ ቅመም፣ በማርና በሻይ ምርት የሚታወቅና ለሀገር ውስጥ ገበያ በማቅረብ ብሎም ኤክስፖርት በማድረግ ከአካባቢው አልፎ ለሀገር አስተዋጽኦ በማድረግ ላይ የሚገኝ መሆኑን ገልፀዋል። አክለውም ዞኑ ከሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች የመጡ በርካታ ብሔር ብሔረሰቦች…

Read More

በክልሉ በሁሉም አከባቢዎች እየተከናወነ ያለው የበጎ ተግባራት ዜጎችን በተጨባጭ ተጠቃሚ እያደረገ ይገኛል:-ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በሁሉም አከባቢዎች እየተከናወነ ያለው የበጎ ተግባራት ዜጎችን በተጨባጭ ተጠቃሚ እያደረገ እንደሚገኝ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ ገልጸዋል። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተደድር ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ እና የኢፌዴሪ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ኤርጎጌ ተስፋዬ በክልሉ በዳውሮ ዞን ታርጫ ከተማ የአቅመ ደካሞች ቤት ግንባታ አስጀምረዋል።…

Read More

የአረንጓዴ አሻራ መርሀግብሩ ሁለንተናዊ የአከባቢ ጥበቃ እና የኢኮኖሚ ዕድገት የሚያሳልጥ ነው። ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል

ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) የሁለተኛው ምዕራፍ አረንጓዴ አሻራ መርሀግብር አካል የሆነው የአንድ ጀምበር የችግኝ ተከላ ዘመቻ በክልሉ በይፋ አስጀምረዋል። በማስጀመሪያ መርሀግብሩ ርዕሰ መስተዳድሩ ባስተላለፉት መልዕክት የአረንጓዴ አሻራ መርሀግብሩ ሁለንተናዊ የአከባቢ ጥበቃ እና የኢኮኖሚ ዕድገት የሚያሳልጥ መሆኑን ገልጸዋል። ከስድስት ዓመታት በፊት በክቡር የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ሀሳብ አመንጭነት ወደ ተግባር የተገባው የአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር የአከባቢ…

Read More

rtrt

በቤንች ሸኮ ዞን ሰሜን ቤንች ወረዳ የሀገር አቀፍ ዘመቻ አካል የሆነው የአንድ ጀምበር የችግኝ ተከላ መርሀ ግብር ተጀምሯል። በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ አቶ ወንድሙ ኩርታ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር የክልሉ መንገድና ትራንስፖርት ቢሮ ሀላፊ አቶ ፋጂዮ ሳፒ ፣ የቤንች ሸኮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሀብታሙ ካፍትንን ጨምሮ ሌሎች የክልል የዞን ከፍተኛ…

Read More

በካፋ ዞን በአንድ ጀንበር ከ5 ነጥብ 2 ሚሊዬን በላይ ችግኝ ለመትከል ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁ ተገለጸ

የካፋ ዞን ግብርና፣ ደን፣ አካባቢ ጥበቃ እና ህብረት ስራ መምሪያ ምክትልና የተፈጥሮ ሀብትና አካባቢ ጥበቃ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ተረፈ ወ/ገብርኤል በ2016 በጀት አመት በካፋ ዞን 74 ሚሊዬን በላይ የተለያዩ የደን እና የፍራፍሬ ችግኞችን በማዘጋጀት 69 ነጥብ 6 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል ታቅዶ ሰፊ ስራ መሰራቱን ተናግረዋል፡፡ በዞኑ እስከአሁን ከ50 ሚሊዮን በላይ ዘርፍ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸውን የተለያዩ…

Read More

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ከ355 በላይ ሄክታር ቢኤች140 የበቆሎ ምርጥ ዘር እያለማ እንደሚገኝ የደቡብ ምርጥ ዘር ድርጅት አስታወቀ

እየለማ ያለው የምርጥ ዘር ብዜት ስራ እየተስተዋለ የሚገኘውን የምርጥ ዘር አቅርቦት እጥረት ለመቅረፍ የሚያስችል መሆኑም ተመላክቷል ። የደቡብ ምርጥ ዘር ድርጅት የማኔጅመንት አካላት በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል እየለማ የሚገኘውን የበቆሎ ምርጥ ዘር ብዜት ስራ ተዘዋውረው ተመልክተዋል ። በምልከታው ላይ የተገኙት የደቡብ ምርጥ ዘር ድርጅት ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ በላይ ሀሪሶ እንደተናገሩት ድርጅቱ የተለያዩ የምርጥ…

Read More

ከአንድ መቶ 12 ሺህ በላይ ማህበረሰብ ክፍሎች በሬድ ፕላስ ኢንቨስትመንት ፕሮግራም ተጠቃሚ መሆናቸው ተገለፀ

REDD+Investment program (የ’ሬድ ፕላስ እንቨስትመንት ፕሮግራም) ኢትዮጵያን ጨምሮ በታዳጊ ሀገሮች ከደን መመንጠርና መመናመን ጋር በተያያዘ ካባቢ አየር የሚለቀቀውን ሙቀት አማቂ ጋዝ ለመቀነስ እንዲሁም በደን ውስጥ የካርበን ክምችትን ለመጨመር በአለም ዓቀፍ የአየር ንብረት ለውጥ ስምምነት ማዕቀፍ ውስጥ የተዘረጋ የፖሊሲ አግባብ እና ውጤት ተኮር ማትጊያ ስርዓት ነው። ፕሮግራሙ በዋናነት በደን አጠባበቅና ልማት እንዲሁም በህብረተሰብ ኑሮ ማሻሻል ላይ…

Read More

በ2016 በጀት አመት በክልሉ ግብርና ቢሮ የምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም የተሻለ አፈፃፀም ማስመዝገብ መቻሉ ተጠቆመ።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ የምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም የ2016 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማና የ2017 ዕቅድ ውይይት በሚዛን አማን ከተማ እየተካሄደ ነው። በመድረኩ ላይ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አማካሪና የጽ/ቤት ቤቱ ኃላፊ አቶ ዮሀንስ መላኩ እንደገለፁት በክልሉ የምግብ ሥርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም ምርታማነትን ለማረጋገጥና በምግብ ራስ ለማስቻል በሚሰራው ሥራ እያበረከተ…

Read More

የደቡብ ምርጥ ዘር ድርጅት በመሬት ናዳና መንሸራተት ለተፈናቀሉ ወገኖች ግምቱ ግማሽ ሚሊየን ብር የሚያወጣ የምግብ እህሎች ድጋፍ አደረገ።

ድጋፉ በካፋ ዞንና በቤንች ሸኮ ዞን በመሬት መንሸራተት ምክንያት ለተፈናቀሉ ወገኖች እንደሚሰጥም ታውቋል። የሰብዓዊ ድጋፉን ይዘው የቀረቡት የደቡብ ምርጥ ዘር ድርጅት ዋና ስራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ በላይ አሪሶ እንደተናገሩት ግምታቸው ግማሽ ሚሊዮን የሚያወጡ የምግብ እህሎችን ለተጎጂዎች ድጋፍ ማድረጋቸውን ተናግረዋል ። ከአቅም በላይ በሆነ የተፈጥሮ አደጋ በመሬት መንሸራተት ሳቢያ የተፈናቀሉ ወገኖችን ባሉበት አካባቢ ቀርቦ በማጽናናት ሰብዓዊነታታቸውን…

Read More