የክልሉ ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ የጤና ተቋማት አገልግሎት ብቃት ማሳደግ ላይ በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ የክልሉ መንግስት ረዳት ተጠሪ አሳሰቡ።
በክልሉ የጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራም አተገባበርን ለማሻሻል የሚመክር መድረክ በታርጫ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል ። በመድረኩ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የክልሉ መንግስት ረዳት ተጠሪ አቶ በላይ ተሰማ አምራች እና ጤናማ ማህበረሰብ የመገንባት ሂደት ስኬታማ ሊሆን የሚችለው የጤና ተቋማት አገልግሎት እና አደረጃጀት ሲገነባ ነው። ስለሆነም በክልሉ በየደረጃ የሚገኙ የመንግስት መዋቅሮችና አደረጃጀቶች እንዲሁም የህብረተሰብ ክፍሎች የዘርፉን ሥራ ውጤታማ ለማድረግ ርብርብ…
