Trendings

ወጣቶች ለሀገረ መንግስት እና ለሰላም እሴት ግንባታ ሚናቸውን በተገቢው ሊወጡ እንደሚገባ ተገለጸ

በካፋ፣ ሸካ እና በቤንች ሸኮ ዞኖች የብልጽግና ፓርቲ የወጣቶች ክንፍ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ” ሀገሬን እገነባለሁ ኃላፊነቴን እወጣለሁ ” በሚል መሪ ቃል ዞን አቀፍ የወጣቶች ውይይት ተካሂዷል። መድረኮቹ ወጣቶች በማህበራዊ፣ በኢኮኖሚና በፖለቲካ ሁኔታዎች ላይ ግልፅ ግንዛቤ እና የጋራ አረዳድ በመፍጠር የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ ዓላማ ያደረገ ነው። ሀገራዊ ለውጡ እንደ ሁሉም የሀገራችን የህብረተሰብ ክፍሎች ወጣቶችን ተጠቃሚ…

Read More

ዶክተር ለገሰ ቱሉ ሸካ ዞን አንድራቻ ወረዳ ገብተዋል

የኢፌዲሪ መንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶክተር ለገሰ ቱሉ በሸካ ዞን አንድራቻ ወረዳ ገብተው የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ይገኛሉ። በወረዳዉ ዮኪጭጭ ቀበሌ በሴቶች አደረጃጀት እየተከናወኑ የሚገኙ የማር መንደርን ጎብኝተዋል። ማህበሩ 78 ዘመናዊ የንብ ቀፎ ያሉት ሲሆን በዓመት 500 ኪ.ግ ማር እንደሚያገኙ፣ማርን ከማምረት ባለፈ በግ፣ፍየል፣በሬ እንደሚያደልቡ፣የበጋ መስኖ ስንዴን በማምረት ተጠቃሚ እየሆኑ መምጣታቸውን በጉብኝቱ ወቅት ተናግረዋል። በ2016…

Read More

የቦንጋ ቀላል የአዉሮፕላን ማረፊያ ግንባታው የተጓተተ በመኾኑ በትኩረት በማጠናቀቅ ወደ አገልግሎት ለማስገባት እንደሚሰራ የኢትዮጵያ ሲቪል አቬሽን ባለስልጣን አስታወቀ

በክልሉ ነባር የአዉሮፕላን ማረፊያዎች ወደ ሥራ ለማስገባት የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ እንዲሚቀጥልም ተገልጿል። በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ከዚህ ቀደመ አገልግሎት ይሰጡ የነባሩና በተለያዩ ምክንያቶች አገልግሎት ያቋረጡ የአውሮፕላን ማረፊያዎችን ዳግም ወደ ሥራ ለማስገባት የተጀመረው ጥረት ተጠናክረው እንደሚቀጥል የኢትዮጵያ ሲቪል አቪየሽን ባለስልጣን አስታወቀ። የኢትዮጵያ ሲቪል አቪየሽን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮሐንስ አበራ እንደገለጹት፥ በክልሉ ከዚህ ቀደመ አገልግሎት…

Read More

የሥራ አጥ ቁጥርን ለመቀነስ የሚከናወኑ ሥራዎች ስኬታማ እንዲሆኑ ድጋፍና ክትትሉ ተጠናክሮ ይቀጥላል – የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር::

በክልሎችና በከተሞች የሥራ አጥ ቁጥርን ለመቀነስ የሚከናወኑ ተግባራት ስኬታማ እንዲሆኑ የሚደረገው ድጋፍና ክትትል ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ዳንኤል ተሬሳ ገለጹ። በአቶ ዳንኤል ተሬሳ የተመራ የሚኒስቴሩ የባለሙያዎች ቡድን በምስራቅ ኢትዮጵያ በሚገኙ ክልሎች በሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ የተሰሩ ሥራዎችን ተዘዋውሮ እየተመለከተ ይገኛል። ቡድኑ በዛሬው ዕለት ከድሬዳዋ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊና አመራሮች ጋር…

Read More

በክልሉ ያለውን ተፈጥሮአዊና ሰብአዊ ሀብቶቻችን ወደ ተጨባጭ ኢኮኖሚ ለመቀየር ልዩ ትኩረት ሰጥቶ መስራት ያስፈልጋል፡፡ ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር)

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የልማት አቅምና ጸጋ መነሻ በማድረግ በተዘጋጀዉ የቀጣይ ሶስት ዓመት ዕቅድ ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ ተጀምሯል። በመድረኩ የተገኙት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) የክልሉ የቀጣይ ሦስት ዓመታት ዕቅዶች ከመደበኛው የአሠራር ስርዓት ለየት ባለ መንገድ ተፈጥሮአዊና ሰብአዊ ሀብቶቻችን ተጠቅመን ወደ ተጨባጭ ኢኮኖሚ ለመቀየር ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ የሚሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የክልሉ የቀጣይ…

Read More

ሙስናና ብልሹ አሰራርን የሚከላከል ማህበረሰብ በመፍጠር በተቋማት ደሞክራሲያዊ አሰራርን ማስፈን እንደሚገባ ተገለጸ

‎”ትውልድን በስነ-ምግባር ተቋምን በአሰራር ” በሚል መሪ ቃል የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ስነ ምግባርና ፀረ ሙስና ዳይሬክቶሬት አዲስ ለተመደቡና ነባር የስነ ምግባር ዳይሬክቶረት ፣ቡድን መሪዎችና ባለሙያዎች የአሰልጣኞች ስልጠና በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ እየተሰጠ ይገኛል። ‎በስልጠናው ማስጀመሪያ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የክልሉ ስነ ምግባርና ጸረ ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ሙሉሰው ዘውዴ እንደገለፁት የሚሰጠው ስልጠና ሙስናና ብልሹ…

Read More

ወደ ማህበረሰቡ ለሚቀላቀሉ የቀድሞ ታጣቂዎች የጤና አገልግሎት መስጠት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ

የጤና ሚኒስቴርና የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን ወደ ማህበረሰቡ ለሚቀላቀሉ የቀድሞ ታጣቂዎች የጤና አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ። መንግስት የቀድሞ ታጣቂዎች ትጥቃቸውን ፈትተው ወደ ማህበረሰቡ በዘላቂነት እንዲቀላቀሉና ሰላማዊ ኑሮ መምራት እንዲችሉ በብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽኑ እየሰራ ይገኛል፡፡ በተለይም የቀድሞ ታጣቂዎች ትጥቅ ከማስፈታት ጀምሮ መልሶ የማቋቋም ስራ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት እየተከናወነ ይገኛል። የቀድሞ ታጣቂዎችን ለሰላምና ምርታማነት ለማዘጋጀትም ማህበራዊ…

Read More

የኩታ ገጠም እርሻ፡ የዳውሮ ዞን አርሶ አደሮችን የልፋት ውጤት እያሳደገ ያለ ስራ

በዳውሮ ዞን ማሪ ማንሳ ወረዳ የሚገኙ አርሶ አደሮች፣ በተናጠል ከሚያካሂዱት እርሻ ወጥተው በኩታ ገጠም (ክላስተር) በመደራጀት የስንዴና ገብስ ምርታቸውን በእጅጉ ማሳደግ መቻላቸውን ተናገሩ። ይህ አዲስ የአሰራር ስርዓት፣ የባለሙያ ድጋፍን ከማቀለሉም በላይ እንደ አረም ያሉ ተግዳሮቶችን በጋራ ለመፍታት በማስቻሉ “የልፋታችንን ዋጋ አግኝተንበታል” ሲሉ አርሶ አደሮቹ ተናግረዋል ። በወረዳው ዳካ የሊ ቀበሌ በሚገኘው “ቦካ ክላስተር” እንደተስተዋለው፣ ቀደም…

Read More

ዘርፉ ለሀገሪቱ ትላልቅ ፕሮጀክቶች አፈፃፀም የላቀ አስተዋፅኦ አበርክቷል – ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር)

የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ዘርፉ ለሀገሪቱ ትላልቅ ፕሮጀክቶች አፈፃፀም የላቀ አስተዋፅኦ አበርክቷል ሲሉ የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) ገለጹ። ሚኒስቴሩ እና ተጠሪ ተቋማት በ2017 በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት ተስፋ ሰጭና አበረታች ስኬቶች ማስመዝገባቸው ተገምግሟል። የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን የኤርፖርት መሠረተ ልማት የመገንባት እና የሀገሪቱን የኤርፖርቶች መዳረሻ የመጨመር፣ የአየር ትራንስፖርት አገልግሎት ተደራሽነትን የማስፋፋት ሥራ መሰራቱ…

Read More

በእንስሳትና ዓሣ ሀብት ልማት ዘርፍ ለከተማ አርቢዎችና ባለሙያዎች የክህሎት ማሻሻያ የአሰልጣኞች ስልጠና እየሰተጠ ነው

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ እንስሳትና ዓሣ ሀብት ልማት ዘርፍ ከምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም ጋር በመተባበር ለከተማ አርቢዎችና ለባለሙያዎች የተዘጋጀ የክህሎት ማሻሻያ የአሰልጣኞች ስልጠና በቦንጋ ከተማ እየተሰጠ ይገኛል። በስልጠናው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክት ኃላፊና የእንስሳትና ዓሣ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ታመነ በቀለ የመድረኩ ዓላማ ለዘርፉ ባለሙያዎች የተሻለ ግንዛቤ ለመፍጠርና የከተማ ግብርና…

Read More