Trendings

ሪፖርታዥ

በክልሉ የግሉ ዘርፍ የኢንቨስትመንት ተሳትፎን ለማሳደግ የሚያስችል ስራ እየተሰራ ነው፦ የክልሉ ንግድና ኢንቨስትመንት ቢሮ የኢንቨስትመንት ዘርፍ ዕድገትና ልማትን በማፋጠን ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ እና የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማሳደግ ሚናው ከፍተኛ ነው፡፡የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ያለውን ፀጋና እምቅ የኢንቨስትመንት አቅም ተጠቅሞ ባለው አቅም ልክ ዘርፉ ለክልሉ ልማትና ዕድገት አስትዋጽኦ እንዲያበረክት በማስቻል፤ በክልሉ ፈጣን ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ለማስመዘገብ የክልሉ…

Read More

የገበታ ለትውልድ ፕሮጀክት የጅማ ከተማን የተደበቀ ውበት ይበልጥ እንዲፈካ አድርጓል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጅማ የነበራቸውን ቆይታ አስመልከተው በሰጡት ማብራሪ ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ሃብት የታደለች ሀገር መሆኗን አውስተው÷ ቢሰራባቸው ዓለምን የሚያስደንቁ የተፈጥሮ ጸጋዎች በሁሉም የኢትዮጵያ ጫፍ እንዳሉ ጠቁመዋል፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ መደመር የሚለው ሃሳብ ሲጀመር ሶስት ዋና ዋና ምሰሶዎች ላይ የቆመ እንደነበር የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ÷ የመጀመሪያው የኢትዮጵያን ተፈጥሮ፣ ጸጋና ሃብት በውል ማወቅ መቻል ነው ብለዋል፡፡ አሁን ላይ የጅማን…

Read More

ከፍተኛ የመንግሥት የስራ ኃላፊዎች የኮይሻ የሃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን ጎበኙ።

የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን፣ የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንትና የጽ/ቤቱ ኃለፊ አቶ አደም ፋራህ፣የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አፈጉባኤ ፣ የፌዴሬሽን ም/ቤት አፈጉባኤ ፣ የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች እና ሚኒስትሮች የኮይሻ የሃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ግንባታ ሥራን ጎብኝተዋል። በአፍሪካ ደረጃ በግዙፍነቱ ሶስተኛ ደረጃ የሆነዉን የኮይሻ ግድብ የንፁህ የኃይል ማመንጨት ስራችንን ያለበት ደረጃ አበረታች መሆኑን…

Read More

የኢትዮጵያ ሴቶች ለሀገራቸው የላቀ አበርክቶ አድርገዋል – ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ

ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን በማስመልከት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። ፕሬዝዳንት ታዬ ቀኑን በማስመልከት በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት የኢትዮጵያ ሴቶች ለሀገራቸው ነፃነት፣ የኢኮኖሚ ዕድገት፣ ማህበራዊ እሴቶችና ባህሎችን ለማፅናት ያበረከቱት አስተዋጽኦ የላቀ ነው ብለዋል። እንቅፋቶችንና ጎታች እሳቤዎችን በመጣል፣ በመላ አቅማቸው የኢትዮጵያን የመዘመን መንገድ ዋነኛ መሪና ተዋናይ መሆናቸውንም ገልጸዋል። ዘንድሮ ቀኑ በዓለም አቀፍ ደረጃ…

Read More

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ኢትዮጵያን ወደ ፈጣን ዕድገት እየመሯት ስለሆነ ሊመሰገኑ ይገባል፡- መሐሙድ አሊ ዩሱፍ

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢትዮጵያን በሁሉም ዘርፍ ወደ ፈጣን ዕድገት እየመሯት ስለሆነ ሊመሰገኑ ይገባል ሲሉ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ተናገሩ፡፡ በኢትዮጵያ እየተካሄደ ባለው 3ኛው የአፍሪካ የሥራ ዕድል ፈጠራ ፎረም መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት ሊቀመንበሩ፤ ኢትዮጵያ በሁሉም ዘርፍ እያመጣች ያለው ለውጥ ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ምሳሌ የሚሆን ነው ብለዋል፡፡ የአፍሪካ ሕዝብ ብዛት…

Read More

በኮንታ ዞን አመያ ከተማ አስተዳደር ከበጋ መስኖ ስንዴ የተሻለ ምርት እንደሚጠብቁ አርሶ አደሮች ገለፁ

የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ከተረጅነት ወደ ምርታማነት መስፈንጠሪያ መሆኑን የወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ገለጸ፡፡ ‎ አርሶ አደር አበሻ ዳሮታ እና ደባልቄ ዳራ በኮንታ ዞን አመያ ከተማ አስተዳደር የጨታ ቀበሌ ነዋሪዎች ሲሆኑ የበጋ መስኖ ስንዴ እያለሙ ከሚገኙ አርሶ አደሮች መካከል ናቸው። ‎ አርሶአደሮቹ የማሳ አረም ስራ ላይ ተሰማርተው ያገኘናቸው ሲሆን በሰጡትም አስተያየት ከባለፈው አመት ጥሩ ተሞክሮ በመውሰድ…

Read More

ከደረጃ “ሐ” ግብር ከፋዮች ከ229 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ተሰብስቧል – ወ/ሮ ህይወት አሰግድ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ህይወት አሰግድ በወቅታዊ የገቢ አሰባሰብ ሂደትን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። በክልሉ ከመነሻው ጀምሮ ሁሉን ባሳተፈ ሁኔታ ከክልል ጀምሮ በየደረጃው አስፈላጊውን መድረክ በመፍጠር በሁሉም ዞኖች የደረጃ “ሐ” የዕለት ገቢ ግመታ ስራ እና የአሰባሰብ ስራዉ በስኬት መጠናቀቁን ተናግረዋል። በተለያዩ ምክንያቶች በየሶስት ዓመቱ መገመት የነበረበት የደረጃ “ሐ” ግብር ከፋዮች…

Read More

#ርፖርታዥ‎ 

በክልሉ ገቢ የመሰብሰብ አቅም ከጊዜ ወደ እየተሻሻለ በመሆኑ የክልሉን የወጭ ፍላጎት በገቢ ለመሸፈን ታልሞ እየተሰራ መሆኑን ወይዘሮ ህይወት አሰግድ ገለፁ። ‎በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ባለፉት ስድስት ወራት ከ8 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን ነው የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ሀላፊ ወይዘሮ ህይወት አሰግድ የገለፁ።‎‎በክልሉ ከተገኘው ገቢ ውስጥ ከ7 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር በላይ የሚሆነው…

Read More

5ኛው የፓኪስታን-አፍሪካ የንግድ ልማት ጉባኤና አውደ ርዕይ በአዲስ አበባ ይካሄዳል

5ኛው የፓኪስታን-አፍሪካ የንግድ ልማት ጉባኤና አውደ ርዕይ ከግንቦት 7 እስከ 9/2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሚሊኒየም አዳራሽ እንደሚካሄድ በኢትዮጵያ የፓኪስታን አምባሳደር አቲፍ ሸሪፍ ሚያን ገለጹ። አምባሳደሩ በሰጡት መግለጫ፥ በንግድ ልማት ጉባኤና አውደ ርዕዩ ላይ ከ100 በላይ የፓኪስታን አምራች ድርጅቶች ይሳተፋሉ ብለዋል። ከአፍሪካ ሀገራት ጋር የንግድ ትስስርን የሚያጠናክሩ የሕክምና መድኃኒት ምርትና መሣሪያዎች፣ የውበትና ቆዳ እንክብካቤ ውጤቶች፣ የጨርቃጨርቅና…

Read More

ለመንገድና ድልድይ ግንባታ የዲዛይን ስራዎች ተገቢውን ትኩረት በመስጠት የፕሮጀክት ውጤታማነትን ማረጋገጥ እንደሚገባ ተመላከተ።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል፣ የመንገዶች ባለስልጣን መስሪያ ቤት፥በክልሉ በአማካሪ ድርጅቶች የተሰሩ የመንገድ እና የድልድይ ፕሮጀክቶች ጥናትና ዲዛይን ሥራ ሪፖርት በቦንጋ ከተማ ግምግሟል። በዲዛይን ግምገማው መድረክ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር አብድዩ መኮንን ለመንገድና ድልድይ ግንባታ የዲዛይን ስራዎች ተገቢውን ትኩረት በመስጠት የፕሮጀክት ውጤታማነትን ማረጋገጥ እንደሚገባ ተናግረዋል። የአንድን ፕሮጀክት ግንባታ ውጤታማነት ለማረጋገጥ የጥናትና ዲዛይን…

Read More