“ኢትዮጵያ ውስጥ ሰው ጋዜጠኛ ወይም ፖለቲከኛ ስለሆነ አይታሰርም”፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው በሰጡት ማብራሪያ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ ውስጥ ሰው ጋዜጠኛ ወይም ፖለቲከኛ ስለሆነ አይታሰርም፡፡ ወደ ፊትም አይታሰርም የፖለቲካ አውዱ ሊሰፋ ይገባል፡፡ በሰዎች መታሰር ኢትዮጵያ ምንም ትርፍ አታገኝም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ግን ደግሞ ህግ መከበርና የህግ የበላይነት መከበር አለበት ብለዋል፡፡ ስልጣን ካልሰጣችሁን፣ ስንታሰር ካልፈታችሁን ምን ዲሞክራሲ አለ ከተባለ እንደዚህ…

Read More

“ኃይልን በማሰባሰብና በመደመር መንገድ ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር ለማሻገር በሚደረገው ጥረት የመምህራን፣ የግብርናና የጤና ባለሙያዎች ሚና የጎላ ነው” – አቶ ኢብራሂም ተማም

በጨና ወረዳ “ኢትዮጵያ ወደ ተምሳሌት ሀገር!” በሚል መሪ ቃል የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫን አስመልክቶ ከትምህርት አመራሮች ፣ ከቀበሌ ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊዎች፤ እንዲሁም የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች ጋር ውጤታማ ውይይት አካሂዷል ። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊና በዋቻ ምርጫ ክልል ለክልል ምክር ቤት ዕጩ ተወዳዳሪ አቶ ኢብራሂም ተማም እንደገለጹት፤ ብልፅግና ፓርቲ ሀገርን መምራት ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ…

Read More

የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን መከበር ለባህል፣ ለቋንቋ፣ ለዲሞክራሲና ለሀገራዊ አንድነት መገንባት ፋይዳው የላቀ መሆኑን የበዓሉ ተሳታፊዎች ተናገሩ

19ኛ የኢትዮጵያ ብሔሮች ብሔረሰቦች እና ህዝቦች በዓል ቀን ክልላዊ ማጠቃለያ መድረክ በተለያዩ ሁነቶች በቴፒ ከተማ ተከብሯል። በበዓሉ ላይ ከክልሉ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተሳተፉ ሲሆን የብሔሮች ብሔረሰቦች እና ህዝቦች በዓል ቀን መከበሩ ለባህል፣ ለቋንቋ፣ ለዲሞክራሲና ለሀገራዊ አንድነት መገንባት ፋይዳው የላቀ መሆኑን ተናግረዋል ። የበዓሉ መከበር አንድነትን የምናጠናክርበትና ብዝሃነት የሚረጋገጥበት ነው ሲሉም አስተያየት ሰጪዎች ተናግረዋል ። በብዝሃነት…

Read More

ከብሔራዊ የደኅንነት ምክር ቤት የተሰጠ መግለጫ

ብሔራዊ የደኅንነት ምክር ቤት ሚያዝያ 1 ቀን 2017 ባደረገው ስብሰባ ሀገራዊ፣ ቀጣናዊና ዓለማዊ ሁኔታዎችን ገምግሟል፡፡ ኢትዮጵያ ለዘመናት ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ እና ዲፕሎማሲያዊ ስብራቶች ገጥመዋት ነበር፡፡ እነዚህን ስብራቶች በመጠገን ወደ ብልጽግና የምታደርገውን ጉዞ እያፋጠነች ትገኛለች፡፡ እስካሁን የጀመረቻቸው ሪፎርሞች እየተሳኩ፤ የወጠነቻቸው ኢኒሼቲቮች ፍሬ እያፈሩ፤ በዓለም አቀፍ መድረኮች ያላት ተሰሚነት እየጨመረ፤ ብሔራዊ ጥቅሞቿን ለማስከበር የምታደርገው ጥረት ውጤት እያስመዘገበ…

Read More

የአረንጓዴ ዐሻራና የተጎሳቆለ መሬት ማገገሚያ ልዩ ፈንድ ማቋቋሚያና አሥተዳደር አዋጅ ጸደቀ

ኢትዮጵያ በደን ዘርፍ ከልማት አጋሮች የምታገኘውን ድጋፍና ጥቅም ለማሳደግ የሚያስችል የአረንጓዴ ዐሻራና የተጎሳቆለ መሬት ማገገሚያ ልዩ ፈንድ ማቋቋሚያና አሥተዳደር አዋጅ ፀደቀ፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 12ኛ መደበኛ ስብሰባ÷ የአረንጓዴ ዐሻራ እና የተጎሳቆለ መሬት ማገገሚያ ልዩ ፈንድ ማቋቋሚያ እና አሥተዳደር አዋጅን በሙሉ ድምጽ አፅድቋል፡፡ የምክር ቤቱ አባላት አዋጁን አስመልክተው በሰጡት አስተያየት÷ ዘላቂ ፈንድ ከማቋቋም…

Read More

በአዲስ አበባ አጀንዳ የማሰባሰብ የምክክር ምዕራፍ ዛሬ ይጀመራል

በአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ምዕራፍ መርሃ ግብር የሚሳተፉ የህብረተሰብ ተወካዮች ወደ ተዘጋጀው ቦታ እየተሰባሰቡ ይገኛሉ። በአዲስ አበባ ከተማ በሚካሄደው የምክክር ምዕራፍ ከ2 ሺህ 500 በላይ ተወካዮች እንደሚሳተፉ የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን መረጃ ያመለክታል፡፡ በምክክር ምዕራፍ መርሃ ግብሩ ሶስት ዋና ዋና ተግባራት የሚከናወኑ ሲሆን እነሱም ተሳታፊዎች በምክክርና በውይይት የአጀንዳ ሀሳቦችን ማምጣት፣ አጀንዳዎቻቸውን የጋራ በማድረግ ያሰባስባሉ፣ ያደራጃሉ እንዲሁም…

Read More

ከ15 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ዜጎች የፋይዳ መታወቂያ አገልግሎት ተመዝግበዋል

በኢትዮጵያ እስካሁን ከ15 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ዜጎች የፋይዳ መታወቂያ አገልግሎት መመዝገባቸውን የብሔራዊ መታወቂያ ኘሮግራም ገልጿል። በዚህ ዓመት መጨረሻም ከ20 እስከ 23 ሚሊዮን ለሚሆኑ ነዋሪዎች የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያን ተደራሽ ለማድረግ እንደሚሰራ የብሔራዊ መታወቂያ ኘሮግራም ምዝገባ ዳሬክተር አቶ ሄኖክ ጥላሁን ለኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ተናግረዋል። አሁን ላይ 5 ሺህ የሚሆኑ የምዝገባ መሳሪያዎችን በመጠቀም አገልግሎቱ እየተሰጠ መሆኑን አቶ…

Read More

በክልሉ በዘንድሮ ዓመት ከ62 ሺህ በላይ ሄክታር ማሳ በበጋ ስንዴ ልማትና በ1ኛ ዙር መደበኛ መስኖ በተለያዩ ሰብሎች ይለማል፦አቶ ማስረሻ በላቸዉ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት ግብርና ቢሮ የ2017 ዓ.ም የበጋ መስኖ ስንዴ ልማትና መደበኛ መስኖ ሥራዎች አፈጻጸም እንዲሁም የ2018 ዕቅድ ዙሪያ የንቅናቄ መድረክ በቦንጋ ከተማ እያካሄደ ይገኛል። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው በወቅቱ እንደገለጹት፤እንደሀገር በምግብ ራስን መቻል፣ተተኪ ምርት ማምረት እና የምግብ ልዑላዊነት ለማረጋገጥ ሥራዎች በትኩረት እየተከናወነ ይገኛል። በሀገራችን…

Read More

sdfv

በዞኑ የበልግ ወቅት የእርሻ ስራ ውጤታማ እየሆነ እንደሆነ ተነገረ በምዕራብ ኦሞ ዞን በሁሉም አካባቢዎች የበልግ ወቅት የእርሻ ስራ ውጤታማ እየሆነ እንደሆነ የዞኑ የግብርና፣ ደን፣ አከባቢ ጥበቃና ህብረት ስራ መምሪያ ገልጿል። ክልሉ ከያዘው የበልግ ወቅት የእርሻ ስራ እቅድ 35-40 በመቶ የሚሆነው የሚሸፈነው በምዕራብ ኦሞ ዞን መሆኑንም የዞኑ ግብርና፣ደን፣ አካባቢ ጥበቃና ህብረት ስራ መምሪያ ኃላፊ አቶ መልኬ…

Read More

የተነደፉ ኢኒሼቲቮችን ከውጤት ለማድረስ አመራሩና ባለሙያው በቁርጠኝነት ሊሰሩ ይገባል፦ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ

በእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት እና በቡና፣ ሻይና ቅመማ ቅመም ልማት ዘርፎች ዙሪያ የንቅናቄ መድረክ ዛሬም ቀጥሎ ውሏል። ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ የዛሬውን መድረክ ሲያጠቃልሉ የግብርና ልማት ስራዎችን ውጤታማ ለማድረግ ተጠያቂነትን ያሰፈነ አሰራር መከተል ይጠበቅብናል ብለዋል። በዘርፉም ተፈጥሮንና የሰውን አቅም በመጠቀም ይበልጥ ለውጤታማነት መትጋት ይገባል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ በሌማት ትሩፋት ስራዎች የተሰጠውን ትኩረት ያህል…

Read More