Trendings

የ24 ዓመቱ የማራቶን ክብረ ወሰን ባለቤት አትሌት ኬልቪን ኪፕቱም ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ::

የ24 ዓመቱ የማራቶን ክብረ ወሰን ባለቤት ኬንያዊው አትሌት ኬልቪን ኪፕቱም በመኪና አደጋ ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱን የዓለም አትሌቲክስ አስታወቀ። ኪፕቱም ባለፈው ጥቅምት ወር ቺካጎ ውስጥ በተደረገ የማራቶን ውድድር 2:00:35 በሆነ ሰዓት በመግባት የዓለም ክብረ ወሰን መስበሩ ይታወሳል። ይኸው ክብረ ወሰን ባለፈው ሳምንት መጽደቁም ይታወቃል። አትሌቱ እና ሩዋንዳዊ አሠልጣኙ ጌርቫይስ ሐኪዚማና ሕይወታቸው ያለፈው ኤልዶሬት ካፕታጋት በተባለ…

Read More

የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የስራ ዕድል ፈጠራ ተግባራትን ከሀገሪቱ የኢኮኖሚ ልማት ስራዎች ጋር ማስተሳሰር ይገባል፦ አቶ ተስፋዬ እንዳሻው ።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ስራና ክህሎት ቢሮ ክልላዊ የክህሎት መር የስራ ዕድል ፈጠራ የንቅናቄ መድረክ በቦንጋ ከተማ ማድረግ ጀምሯል። በንቅናቄው መድረክ የተገኙት የክልሉ ስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ተስፋዬ እንዳሻው ገበያ መር የክህሎት ልማትን እውን በማድረግ ሁለንተናዊ ብልጽግናን በማረጋገጥ ዜጎች ፍትሐዊ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ቢሮው ተልዕኮውን እየተወጣ ይገኛል ብለዋል። ሀገራዊ ለውጡን ውጤታማ፣ዘላቂና ተቋማዊ በማድረግ ክልላዊ…

Read More

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ከ700 በላይ ቀበሌዎች የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ በዲጂታል ምዝገባ ሥራ / Online / ውስጥ እንዲገቡ ተደርጓል፡፡

የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ተግባራትን ለማሳካት እንዲቻል ከ2 ሚሊዮን 443 ሺህ 600 ብር በላይ የሚገመት የኤሌክትሮኒክስ ግዥ መፈጸሙም ተገልጿል ፡፡ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት ሠላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊና የወሳኝ ኩነቶች ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሰለሞን ደነቀ እንደገለጹት የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባን በክልሉ በሚገኙ ሁሉም መዋቅሮች ወደ ድጅታል ምዝገባ ሥራ /Online / ውስጥ እንዲገቡ…

Read More

በብልጽግና ፓርቲ በክልሉ ባለፉት ዓመታት በፖለቲካው ዘርፍ በርካታ ተግባራት ተከናዉኗል፡፡ አቶ ነጋ አበራ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የፖለቲካ እና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ነጋ አበራ፤ ብልጽግና ፓርቲ በአንደኛው መደበኛ ጉባኤ ካስቀመጣቸው ውሳኔዎች እና ክልሉ ከተመሠረተ ወዲህ የፓርቲው ተግባራትን አስመልክቶ ለሚዲያዎች ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። አቶ ነጋ አበራ በጋዜጣዊ መግለጫቸውም ብልጽግና ፓርቲ በክልሉ ባለፉት ዓመታት በፖለቲካው ዘርፍ በርካታ ዘርፍ ብዙ ተግባራት ማከናወን መቻሉን ተናግረዋል።…

Read More

በመፍጠንና በመፍጠር እሳቤዎች ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ ከወትሮው በተለየ መልኩ መትጋት ያስፈልጋል፦ አቶ ፍቅሬ አማን

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የ2017 ዓ.ም የስድስት ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ ከዘርፉ አመራሮች ጋር አካሂዷል። በመድረኩ ባለፉት ወራት በፓርቲው የእሳቤዎች ቅኝት የተከናወኑት ተግባራት የነበሩ ጥንካሬዎች የተፈተሹበት ፣እጥረቶችን ነቅሶ በመለየት ሰፋ ያለ ውይይት ተካሂዷል። በፓርቲው እሳቤዎችና መርህ ላይ የተቃኘ ለሁለንተናዊ የብልፅግናን ጉዞ ስኬት መሰረት የሚጥሉ ተግባራት መከናወናቸው ተገልጿል። በዚህም ጠንካራ ፓርቲ፣ ጠንካራ…

Read More

ሁሉንም የገቢ አርዕስቶች ለይቶ በአግባቡ በመሰብሰብ የህብረተሰቡን የልማትና መልካም አስተዳደር ጥያቄ ለመመለስ መረባረብ ያስፈልጋል፦አቶ አበበ ማሞ

የሸካ ዞን ገቢዎች መምሪያ የ6 ወራት ዕቅድ አፈፃፀምና በቀሪ ወራት ትኩረት አቅጣጫ ዙሪያ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት የምክክር መድረክ በማሻ ከተማ እያካሄደ ይገኛል። የሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አበበ ማሞ በመድረኩ ላይ ተገኝተው ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር ገቢ ኢኮኖሚያዊ ፣ማህበራዊና ፖለቲካዊ ስራዎችን ለማሳካት ትልቅ ድርሻ አለው ብለዋል። በዞኑ በ2017 በጀት ዓመት ከ1.1 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ…

Read More

ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሟን በሚያስከብሩ ጉዳዮች ላይ በንቃት እንደምትሳተፍ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ

ኢትዮጵያ በአፍሪካ ሕብረት ጉባኤ እና በጣሊያን-አፍሪካ ጉባኤ ላይ ብሔራዊ ጥቅሞቿን በሚያስጠብቁና ከፍ በሚያደርጉ ጉዳዮች ላይ በንቃት ለመሳተፍ መዘጋጀቷን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ። የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ በሰጡት መግለጫ እንዳመለከቱት፣ በአዲስ አበባ በሚካሄዱት ጉባኤዎች የሀገራት መሪዎች፣ ሚኒስትሮችና፣ ከፍተኛ ዲፕሎማቶችን ጨምሮ በርካታ ቁጥር ያላቸው እንግዶች ይታደማሉ። ኢትዮጵያም ይህንን አጋጣሚ ብሔራዊ ጥቅሟን ለማስከበርና ተሰሚነቷን…

Read More

ታሪካዊ የባሕር በር መብታችንን ለማረጋገጥ የበኩላችንን እንወጣለን፡- ብሔራዊ የኢትዮጵያ ሠራዊት ማኅበር

ብሔራዊ የኢትዮጵያ ሠራዊት ማኅበር ወቅታዊ በሆነው የሀገሪቱ የባሕር በር አጀንዳ ላይ የፓናል ውይይት አካሄደ። በውይይቱ ላይ የማኅበሩ አባላት፣ የሃይማኖት አባቶች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። የማኅበሩ ፕሬዚዳንት ብርሃኑ አማረ በመድረኩ ባደረጉት ንግግር፤ የባሕር በር ጉዳይ ሀገራዊ አጀንዳ እንዲሆን በማድረጋቸው ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ምስጋና አቅርበዋል። “ኢትዮጵያና ቀይ ባሕር ተነጣጥለው አያውቁም” ያሉት ፕሬዚዳንቱ፤ በታሪክ አጋጣሚ…

Read More

3ኛ ዙር የኢትዮጵያ ታምርት ኤግዚቢሽን እና ባዛር ተከፈተ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ኢንዱስትሪና ኢኖቬሽን ቢሮዉ የተዘጋጀዉ 3ኛው ዙር ክልል አቀፍ የኢትዮጵያ ታምርት ኤግዚቢሽን እና ባዛር በርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ በሚዛን አማን ተከፍቷል ። አምራች ኢንዱስትሪው ኢኮኖሚያዊ ብዝሃነትንና ዕድገትን በማጎልበት ኢትዮጵያን መካከለኛ ገቢ ካላቸው ሀገራት ተርታ ለማሰለፍ ወሳኝ ነው። ዘመናዊ ኢንዱስትሪ በኢትዮጵያ ያለውም ከ1945 ዓ/ም ጀምሮ መሆኑን ታሪክ ያስረዳል። ከዚያን ጊዜ…

Read More

የክልሉ መንግስት መስተዳድር ምክር ቤት 47ኛ መደበኛ ስብሰባዉን በሃለላ ኬላ አካሂዷል።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት መስተዳድ ምክር ቤት ዛሬ በሃላላ ኬላ ባካሄደዉ 47ኛዉ መደበኛ ስብሰባ በ1ኛ አጀንዳነት የተመለከተዉ የክልሉ መንግስት የአስፈጻሚ ተቋማት የበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ስድስት ወራት አፈጻጸም ገምግሞ ቀጣይ አቅጣጫ በማስቀመጥ በመሉ ድምጽ አጽድቋል። ምክር ቤቱ በ2ኛ አጀንዳነት የመንግስት ፍርድ ቤቶች የዳኝነት አገልግሎት ለመወሰን የወጣ ረቂቅ ደንብ ላይ ተወያይቶ አስተያየት በመስጠት ወደ ምክር…

Read More