Trendings

ከስራ ዕድል ፈጠራ አኳያ የክልሉ መንግስት በሰጠው ልዩ ትኩረት ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ውጤታማ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ የስራና ክህሎት ቢሮ አስታወቀ።

የቢሮው ሀላፊ ዶ/ር ዐብይ አንዴሞ ቢሮው በክልሉ በ2018 በጀት አመት 10 ወራት ውስጥ የዜጎችኝ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ማከናወኑን ተናግረዋል። ሀላፊው አክለውም ከስራ ዕድል ፈጠራ አኳያ በግብርና፣በኢንዱስትሪና አገልግሎት ዘርፎች በአጠቃላይ ለ62 ሺ 72 ዜጎች የስራ ዕድል መፈጠሩንም አብራርተዋል። የቢሮው ምክትል ሀላፊና የስራ እድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት ዘርፍ ሀላፊ አቶ ዳዊት ወንድሙ በበኩላቸው ቢሮው ከፋይናንስ አቅርቦት አንፃር…

Read More

የሚዛን አማን ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የመማር ማስተማር ሂደት ተጎበኘ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ተማም በሚዛን አማን ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ያለውን የመማር ማስተማር እና የተግባር ማሰልጠኛ ክፍሎችን ጎብኝተዋል። ኮሌጁ ተማሪዎች ወደ ሥራ ከመሰማራታቸው በፊት በቂ ክህሎት እንዲጨብጡ እያደረገ ያለው ጥረት የሚበረታታ መሆኑ ተገልጿል። ብቁ የጤና ባለሙያዎችን ለማፍራት የንድፈ-ሀሳብ ትምህርቱን ከተግባር ጋር ማቀናጀቱ ለጤናው ዘርፍ ዕድገት ወሳኝ መሆኑ ተመልክቷል። የመማር…

Read More

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ምሩቃን ቀን ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በተገኙበት እየተከበረ ነው

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ምሩቃን ቀን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በተገኙበት በስድስት ኪሎ ካምፓስ እየተከበረ ነው። በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር)፥ ዩኒቨርሲቲው ላለፉት 74 ዓመታት በርካታ ምሁራንን ማፍራቱን ገልፀዋል። ዩኒቨርሲቲው በተለያዩ ዘርፎች የተሰማሩ ምሁራንን ከማፍራትም ባለፈ በጥናትና ምርምር ዘርፍ ለሀገር የላቀ አስተዋጽኦ ማበርከቱንና አሁንም ይህንኑ አጠናክሮ መቀጠሉን ገልፀዋል።…

Read More

በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን ምርት ጥራት ምርመራና ሴርተፊኬሽን ማዕከል በቦንጋ ከተማ ዳግም ሥራ መጀመሩን የማዕከሉ አደራጅ አብይ ኮሚቴ አስታወቀ።

ማዕከሉ ዳግም መከፈቱ ከዚህ ቀደም በተለያዩ አካባቢዎች ላይ በነጋዴዎች ላይ ይደርስ የነበረዉን ጫና የሚቀነስ ነዉ ስል የካፋ ዞን ቡና አቅራቢዎች እና አዘጋጆች ማህበር ገልጿል። የካፋ ዞን ግብርና፣ ደን፣ አከባቢ ጥበቃና ሕብረት ሥራ ልማት መምሪያ ኃላፊና የቦንጋ ምርት ጥራት ምርመራና ሴርተፊኬሽን ማዕከል አብይ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ጋዎ አባመጫ ቡና ለዞኑ ማህበረሰብ ከባህላዊና ታሪካዊ ቁርኝት ባለፈ ማህበራዊና…

Read More

የብሔራዊ ቤተመንግስት ሙዚየም ለህዝብ ክፍት ሆነ

እድሳት ተደርጎለት ላለፉት 4 ወራት በሙከራ ስራ ላይ የቆየው የብሔራዊ ቤተመንግስት ሙዚየም ከዛሬ ጀምሮ ለህዝብ ክፍት ተደርጓል፡፡ ቤተመንግስቱ ጥንታዊ ተሽከርካሪዎችና መካነ እንስሳትን ጨምሮ በውስጡ በርካታ ታሪካዊ ቅርሶችን የያዘ ሲሆን፥ ደረጃቸውን የጠበቁ ሬስቶራንቶችና ስፓዎች ይገኙበታል፡፡ ሙዚየሙ ክፍት መደረጉን አስመልክተው የብሔራዊ ቤተመንግስት ዋና አስተዳዳሪ አቶ ምትኩ ደሬሳ በሰጡት መግለጫ፥ ቤተመንግስቱ ኢትዮጵያን ከተረጂነት ለማላቀቅ ትልቅ ሚና እንዳለው አንስተዋል፡፡…

Read More

ሪፖርታዥ

የክልሉ  ጠቅላይ ፍርድ ቤት የስራ እንቅስቃሴ ፍርድ ቤት ከሦስቱ የመንግስት አካላት ማለትም የህግ አውጪ፣  ህግ አስፈፃሚ እና ህግ ተርጓሚ  አካል አንዱ ሲሆን በህግ አውጪ የወጣውን ህግን የመተርጎም ተግባር የሚያከናወን፣ ዳኝነት የመስጠት ስልጣን ያለው አካል ነው። ፍርድ ቤት በፈደራልም ሆነ በክልሉ መንግስት የወጡ ወንጀል ህግ፣ የፍትሐብሔር ህግ፣ አስተዳዳራዊ ህግ እና ሌሎችን ህጎችን በሥነ-ሥርዓት ህጎች መሠረት በገለልተኝነት…

Read More

በክዋኔና በአካባቢ ኦዲት ግኝት አመላለስ ውጤታማነት የባለድርሻ አካላት በቅንጅትና ቁርጠኝነት መወጣት አለባቸው ፦ የተከበሩ አቶ ወንድሙ ኩርታ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት ፋይናንስ ቢሮ ከክልሉ ምክር ቤት ኦዲት ግኝት አስመላሽ ግብረ-ኃይል ጋር በክዋኔና በአካባቢ ኦዲት ግኝት አመላለስ ዙሪያ የምክክር መድረክ በቦንጋ አካሂደዋል። ለመድረኩ ላይ በክዋኔና በአካባቢ ኦዲት ግኝት የእርምት እርምጃ አወሳሰድ ያለበት ደረጃ ለመከታተል የተዘጋጀ ቼክ ሊስት ዋና ኦድተር ጀኔራል አቶ አስራት አበበ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል። ዓላማውም በኪዋኔና በአካባቢ ኦዲት ግኝት…

Read More

ስልጠናው የአመራሩን የመፈጸምና የማስፈጸም አቅም ከመገንባት ባሻገር ሀገራችንና ክልላችን ወደ ተሻለ ምዕራፍ ለማሸጋገር ትልቅ ስንቅ የተያዘበት መድረክ ነው ፦አቶ ማስረሻ በላቸው

‎ ‎”ከመልካም አመራርነት ወደ ታላቅ አመራርነት መሻገር ” በሚል መሪ ቃል ሲሰጥ የነበረዉ ስልጠና ተጠናቋል። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ከአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ጋር በመተባበር ባለፉት ሦስት ተከታታይ ቀናት ስሰጥ የቆየው የአመራር ስልጠና መድረክ ለቀጣይ ተልዕኮ ዝግጁነትና ቁርጠኝነት በመፍጠር በስኬት ተጠናቋል። ‎ ‎የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው በስልጠናው ማጠቃለያ…

Read More

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት 9ኛ መደበኛ ጉባኤውን የካቲት 5 እና 6 እንደሚያካሄድ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ የተከበሩ አቶ ወንድሙ ኩርታ ገልፀዋል።

የ2018 ዓ.ም ግማሽ ዓመት የአስፈፃሚ አካላት ስራ ሪፖርትን ጨምሮ ሌሎች አጀንዳዎች በጉባኤው እንደሚቀርቡም አመላክተዋል። ከጉባኤው አስቀድሞ ምክር ቤቱ በቋሚ ኮሚቴና በጽ/ቤት አማካኝነት በግማሽ ዓመት ለማከናወን ካቀዳቸው ተግባራት መካከል በተለይም የድጋፍና ክትትል እንዲሁም የቁጥጥር ስራዎችን በ5ቱም ዘርፍ ሰርቶ ማጠናቀቁን የተከበሩ አፈ-ጉባኤ አሳውቀዋል። በተጨማሪ የቋሚ ኮሚቴ ስራ ሪፖርት ተገምግሞ ግብረ መልስ ተሰጥቷል ብለዋል። ከግምገማው በኋላ እንደ ክልል…

Read More

ለክልሉ ጂምናስቲክ ልዑካን ቡድን አቀባበል ተደረገለት::

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልልን በመወከል በኢትዮጵያ ጂምናስቲክ ሻምፒዮና ውድድር ላይ ተሳትፈው ስምንት መዳልያዎችንና አንድ ዋንጫ በማግኘት ውድድሩን ያጠናቀቀው ልዑካን ቡድን ቦንጋ ከተማ ሲደርስ አቀባበል ተደርጎለታል። በአቀባበል መርሐግብሩ ላይ የክልሉ ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ምክት ኃላፊና የስፖርት ዘርፍ ኃላፊ አቶ አህመዲን አወል፣ የክልሉ ጂምናስቲክ ፌደሬሽን ም/ፕሬዝዳንት አቶ አንተነህ አየለ እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።…

Read More