የሕብረት ሥራ ማህበራትን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ሪፎርም ለማካሄድ ዝግጅት እየተደረገ ነው – የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል መንግስት ሕብረት ሥራ ኤጀንሲ::
የሕብረት ሥራ ማህበራትን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ሪፎርም ለማካሄድ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል መንግስት ሕብረት ሥራ ኤጄንሲ ገለጸ። በአንድ ሺህ መሠረታዊ ማህበራት ላይ ሪፎርም እንደሚደረግ ተጠቁሟል። በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል 2069 መሠረታዊ ማህበራትና 21 ዩኒየኖች ይገኛሉ። የሪፎርሙ ዓላማ የሕብረት ስራ ማህበራትን ተወዳዳሪ ለማድረግ፣ ምርትና ምርታማነትን ለመጨመር፣ የፋይናንስ አቅማቸውን ለማሳደግ፣ አሰራርን ለማሻሻልና የአባላትን…
