ዜጎች የጡረታ መብታቸውን የሚከበርበትን አሰራር በማሻሻል በአጭር ጊዜ መብታቸውን የሚያስከብሩበት ሁኔታ ማመቻቸቱን የግል ድርጅት ሠራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር አስታወቀ
በኢፌዴሪ የግል ድርጅት ሠራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር የጅማ ድስትሪክት በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ከባለድርሻ አካላት ጋር በቦንጋ ከተማ መክሯል። በምክክሩ መድረክ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ተስፋዬ እንዳሻው ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደሩ ሰላማዊ የኢንዱስትሪ ግንኙነቶችን በመፍጠር ከመንግስት የተሰጠውን ተልዕኮ እየፈጸመ ይገኛል ብለዋል። በዚህም በአሰሪና ሰራተኞች መካከል ጤናማ የስራ ግንኙነት…
