የአማራ ክልልን ወደ ሰለማዊ እንቅስቃሴ ለመመለስ የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ አስታወቀ
በአማራ ክልል እየተከናወነ ያለው የሕግ ማስከበር ተግባር በአጭር ጊዜ በማጠናቀቅ ክልሉን ወደ ሰለማዊ እንቅስቃሴ ለመመለስ የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ አስታወቀ። በአማራ ክልል ያጋጠመውን የፀጥታ መደፍረስ በመደበኛ የሕግ ማስከበር ሥርዓት ለመቆጣጠር አዳጋች ሆኖ በመገኘቱ የፌዴራል መንግሥት አስፈላጊውን የሕግ ማዕቀፍ እንዲተገብር የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት መጠየቁ ይታወሳል። ይህን ተከትሎም የሚኒስትሮች ምክር…
