እንደ ሰንደቅ ዓላማ ያሉ የጋራ እሳቤ የሚያሰርጹ፣አንድነታችን እና አብሮነታችን የሚያስተሳስሩ የጋራ ጉዳዮችን በየጊዜው መዘከር እና ከፍ ማድረግ ይገባናል -ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ( ዶ/ር)
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የብሔራዊ ሰንደቅዓላማ ቀን በተለያዩ ስነ-ሥርዓቶች በቦንጋ ከተማ ተከብሯል። በክልሉ የዘንድሮ 18ኛው የሰንደቅ ዓላማ ቀን ”ሰንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብስራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ህዳሴ!” በሚል መሪ ሀሳብ ተከብሮ ውሏል። በአከባበር ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ እንደገለፁት፤ ኢትዮጵያ ብዙ ብሔር ብሔርሰቦችና ህዝቦች የሚገኙባት ምንም…
