Trendings

የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ መልዕክት

የመንግስት ተቋማትን የመጀመሪያ ሩብ አመት የ100 ቀናት የሪፎርምና ዋና ዋና የኢኮኖሚ ዕቅድ አፈጻጸም ዛሬ መገምገም ጀምረናል፡፡ በቆይታችንም በ100 ቀናት የትኩረት ማዕከል የሆኑ አበይት ተግባራት ላይ የተገኙ ዉጤቶችን እና የታዩ ክፍተቶችን ከተቋማቱ የስራ ኃላፊዎች ጋር በጋራ እናያለን፡፡ የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት አፈጻጸም ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ቀርቦ ውይይት እንደተደረገበት አይዘነጋም፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር…

Read More

የመደመር መንግስት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሀገራዊ የብልጽግና ጉዞ ላይ አይተኬ ሚና እንዳላቸው በጽኑ ያምናል፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

የመደመር መንግስት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሀገራዊ የብልጽግና ጉዞ ላይ አይተኬ ሚና እንዳላቸው በጽኑ እንደሚያምን እና ለተግባራዊነቱም እየሰራ እንደሚገኝ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ሀሳብ የለውጥ ኃይል ነው።ምሁራን ደግሞ የለውጥ ወኪሎች ናቸው ብለዋል። ምሁራን በማኀበረሰብ ውስጥ የሚፈጥሩት ለውጥም ሀገርን ወደ ብልጽግና እንደሚወስድ ጠቅሰው፥ በዚህ ረገድም…

Read More

ከ3 ነጥብ 4 ሚሊየን ብር በላይ የካፌቾ ብሔር የዘመን መለወጫን በጋራ ለማክበር በተደረገው ንቅናቄ ተሰብስቧል፦ የካፋ ዞን አስተዳደር

የዘንድሮውን የካፌቾ ብሔር የዘመን መለወጫ በጋራ ለማክበር እየተደረገ ባለዉ የገቢ አሰባሰብ በእስካሁኑ ከ3 ነጥብ 4 ሚሊየን ብር በላይ መሰብሰቡን የካፋ ዞን አስተዳደር ገለጸ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳሻው ከበደ በቀደምት አባቶች ገለዜ አንስቶ በየዓመቱ እየተከበረ ለብዙ ዘመናት የቆየውን የካፌቾ ብሔር የዘመን መለወጫ በዓል ለማክበር የተለያዩ ዝግጅቶች እየተደረጉ ነዉ ብለዋል። በበዓሉ በተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ የብሔሩ ተወላጆች…

Read More

አጦ መንትያ ተራራ፡ የዳውሮው ግርማ ሞገስና የሃላላ ኬላው ዘብ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ፣ የዳውሮ ዞን ልብ ውስጥ፣ አንድ ግርማ ሞገስ የተላበሰ ተራራ የንጉሥ ሃላላ ኬላን ታሪካዊ ስፍራ ከፍ ብሎ በትኩረት የሚጠብቅ ይመስላል። ይህ በሎማ ቦሣ ወረዳ የሚገኘውና የአካባቢው ድምቀት የሆነው ተራራ አጦ መንትያ ይሰኛል። ከባህር ጠለል በላይ በ3 ሺህ ሜትር ከፍታው የሰማይ ጉልላትን የሚዳስስ የሚመስለው ይህ ተራራ፣ ከ17 ሺህ ሄክታር በላይ በሆነው ሰፊ ግዛቱ አስደናቂ…

Read More

በሕገ-ወጥ ድርጊት በሚሳተፉ አካላት ላይ የሚወሰደው ርምጃ ተጠናክሮ ይቀጥላል፦አገልግሎቱ

በሕገ-ወጥ ድርጊት በሚሳተፉ አካላት ላይ የሚወሰደው ርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የፋይናንስ ደኅንነት አገልግሎት አስታወቀ፡፡ አገልግሎቱ በሰጠው መግለጫ÷ የፋይናንስ ወንጀሎች በሀገር ላይ የሚያደርሱት ጉዳት ዘርፈ ብዙ እና ከፍተኛ መሆኑን አስረድቷል፡፡ በመሆኑ ኢትዮጵያ ወንጀሎቹን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የተለያዩ ህጎችን አውጥታ በመተግባር እንደምትገኝም አስገንዝቧል፡፡ ለአብነትም በወንጀል ድርጊት የተገኘ ገንዘብ ወይም ንብረት ህጋዊ አስመስሎ የማቅረብና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣው…

Read More

ወደብን በሚመለከት!

የወደብ ጉዳይን አዲስ ጥያቄ አድርገው የሚያነሱ አሉ፤ የጎረቤት አገራትን ሉዓላዊነት ለመጉዳት የተነሳም አስመስለው የሚያቀርቡ አሉ፡፡ ነገር ግን ኢትዮጵያ የማንንም አገር ሉዓላዊነት የመጉዳትና የመውረር ፍላጎት የለንም፡፡ ኢትዮጵያ ያልተገባ ጥያቄ ከህግ ውጪ አልጠየቀችም፡፡ ኢትዮጵያ ወደ ጎረቤት አገራት አንድ ጥይት የመተኮስ ፍላጎትም የላትም፡፡ ነገር ግን በህግና በቢዝነስ ማእቀፍ እንወያይ ነው ያልነው፡፡ የኢትዮጵያ ህዝብ እያደገ ነው፤ በመሆኑም ጉዳዩ ጊዜ…

Read More

በቦንጋ ከተማ የመንገድ ዳር መብራት ሽቦ የሰረቀ ተከሳሽ እና የተሰረቀ ሽቦዎችን ከሌባ የገዛ አንድ ግለሰብ በእስራትና በገንዘብ መቀጣታቸዉን በካፋ ዞን ፍትህ መምሪያ አስታወቀ

ወንጀሉ የተፈጸመው በካፋ ዞን በቦንጋ ከተማ አስተዳደር ጥር 7 ቀን 2016 ዓ.ም ከንጋቱ 12:00 ሰዓት በዩንቨርስቲ ቀጠና አበቺ መንደር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ሲሆን ወንጀሉን የፈፀሙት ታረቀኝ ቆጭቶና ታምራት ወ/ማሪያም መሆናቸዉን የገለፁት በካፋ ዞን ፍትህ መምሪያ የታክስና ኢኮኖሚ ነክ ወንጀሎች ዐቃቤ ህግ አንዷአለም አሰፋ ናቸዉ። እንደ ዐቃቤ ህግ አንዷአለም ገለፃ ተከሳሽ ታረቀኝ ቆጭቶ የተባለው በተጠቀሰው ቀን…

Read More

የክልሉ ምክር ቤት 6ኛው ዙር 4ኛ የስራ ዘመን 8ኛ መደበኛ ጉባኤ በ2ኛ ቀኑ የአስፈጻሚ አካላት የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ተወያይቶ አፅድቋል።

በውይይቱ ከምክር ቤቱ አባላት የተለያዩ ጥያቄዎችና በግብዓትነት የሚወሰዱ ሀሳቦች ተነስተው ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል። ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ ከምክር ቤት አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች ማብራሪያ ሰጥተዋል። ከምክር ቤቱ አባላት የቀረቡ አስተያየቶች እና ጥያቄዎች አስተማሪና በዝርዝር ዕቅድ በማካተት በቀጣይ የሚከናወኑ መሆናቸውንም ርዕሰ መስተዳድሩ ተናግረዋል። የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ያባለፈው ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምን መነሻ በማድረግ የተዘጋጀና እስካሁን…

Read More

በክልሉ ያሉ የደን ሀብቶች ላይ ሊተገበር የታሰበው ፕሮጀክት እንዲሳካ ባለድርሻ አካላት የሚጠበቅባቸውን ሁሉ ሊወጡ እንደሚገባ ተገለጸ።

የደን ሀብት ዲጂታል መረጃ የማደራጀት እና ለውሳኔ እንዲያገለግሉ መረጃዎች የሚደራጁበት የጥናትና ምርምር መርሃ ግብር የፕሮጀክት ግምገማ ተጠናቋል ። ክልላዊ የደን ሀብት መረጃን ወደ ድጂታል በመቀየር ሚዛናዊ የሆነ የደን ሀብት ሊያሳይ የሚችል መረጃ ማደራጀት ይገባልም ተብሏል። በዚህ ግምገማ የተገኙ ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት በክልሉ ህብረተሰቡ ለደን የሰጠው ዋጋ በውል ባለመታወቁ ተጠቃሚ መሆን እንዳልቻሉ ተናግረዋል ። የተጠናው ፕሮጀክት…

Read More