ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች፡-
2017 ዓ.ም ይቻላል ተብለው ያልታሰቡ ጉዳዮች የተከናወኑበት እና የስኬት ዓመት ነበር፣ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የግብርና መር ፖሊሲ ይከተል ነበር ይህንን ወደ ብዝሀ ዘርፍ ቀይረን በእጅጉ ውጤታማ ሆነናል፣ በአንድ ሴክተር ላይ ተንተርሶ መስራት ከድህነት አረንቋ ስለማያወጣን ብዝሀ ዘርፍን በመከተላችን ውጤት አምጥተናል፣ ግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ማዕድን፣ ቱሪዝም እና ቴክኖሎጂ እነዚህ አምስት ግንባር ቀደም ሴክተሮች ብዝሀ ዘርፍ ሆነው ቢመሩ የኢትዮጵያን…
