Trendings

በግብርናው ዘርፍ የሴቶችና አካል ጉዳተኞችን ተሳትፎና ፍትሃዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ የዘርፉን ውጤታማነት ለማስቀጠል የማይተካ ሚና እንዳለዉ ተገለጸ

የግብርና ሚኒስቴር ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ አካቶ ትግበራ ስራ አስፈፃሚ ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ ስርዓተ-ፆታና ኤች አይ ቪ ኤድስ ሜንስትሪምንግ ጋር በመቀናጀት ለክልሉ ግብርና ቢሮ የስራ ኃላፊዎች፤ መንግስታዊ ላልሆኑ ድርጅቶችና ፕሮግራሞች በስርዓተ-ፆታና ማህበራዊ ጉዳይ ተሳታፊነትና ተጠቃሚነት ዙሪያ የተዘጋጀዉ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል፡፡ የዉይይት መድረኩ ዋነኛ ዓላማ በሥርዓተ-ፆታና ማህበራዊ ጉዳዮች አካቶ…

Read More

በግርማ አመንቴ (ዶ/ር) የተመራ ልዑክ በብራዚል የሥራ ጉብኝት እያደረገ ነው::

በግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) የተመራ የኢትዮጵያ ልዑክ በብራዚል የሥራ ጉብኝት እያደረገ ነው። የልዑካን ቡድኑ አባላት ጉብኝት በብራዚል በግብርናው ዘርፍ የተሰሩ ሥራዎችን ልምድ ለመቅሰም ያለመ መሆኑ ተገልጿል፡፡ በብራዚል በምርትና ምርታማነት ላይ ያጋጠሙ ተግዳሮት የተፈቱባቸው ዘዴዎችን እና የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም በምርት ዕድገት ላይ አዎንታዊ እመርታ ማስመዝብ የተቻለበት ሒደትንም ልዑኩ ተመልክቷል፡፡ የብራዚል መንግስት የዜጎችን የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ…

Read More

የዜጎችን ሁለንተናዊ ኑሮ ለማሻሻል በተከናወኑ የማኅበራዊ ዘርፍ ተግባራት አበረታች ውጤት መመዝገቡ ተገለጸ።

በበጀት ዓመቱ አንደኛው ሩብ ዓመት በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የዜጎችን ሁለንተናዊ ኑሮ ለማሻሻል በተከናወኑ የማኅበራዊ ዘርፍ ተግባራት አበረታች ለውጥ መመዝቡ ተገልጿል። ይህ የተገለጸው የክልሉ ፕላንና ልማት ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ወሰነች ቶማስ፤ የክልሉን የ2018 የአንደኛው ሩብ ዓመት የአፈጻጸም ሪፖርት ባቀረቡበት ወቅት ነው። በጤናው ዘርፍ በበጀት ዓመቱ፥ የማዐጤመ አግልግሎት ለማሻሻል ከ139 ሚሊዮን ብር በላይ ገንዘብ ለ121…

Read More

በብልጽግና ፓርቲ መሪነት በክልሉ ውስጥ የተከናወኑ የልማት ስራዎችን የሚያሳይ የፎቶ አውደ-ርዕይ ተጎበኘ

“የሀሳብ ልዕልና ለሁለንተናዊ ብልጽግና!” በሚል መሪ ቃል የሚከበረው የብልጽግና ፓርቲ 5ኛ ዓመት የምስረታ ክብረ በዓል ክልላዊ የማጠቃለያ መድረክ በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። በዓሉ ከታችኛው የፓርቲ መዋቅር ጀምሮ እስከ ክልል ተቋማት ድረስ በተለያዩ ኩነቶቸ እየተከበረ የመጣ ነው፡፡ በደም ልገሳ ፣ በከተማ ጽዳት ፣ የባለፉት የፓርቲው ስኬቶችን አውደርይ በማዘጋጀትና ለሕዝብ በማስተዋወቅ እንዲሁም የበጎ አድራጎት ተግባራትን ማከናወን ተጠቃሾች…

Read More

በፓሪስ ኦሎምፒክ ውድድር ኢትዮጵያ የላቀ ውጤት እንድታስመዘግብ ዝግጅት እየተደረገ ነው::

በፈረንሳይ ፓሪስ በሚካሄደው ኦሎምፒክ ውድድር ኢትዮጵያ የላቀ ውጤት እንድታስመዘግብ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ አስታወቀ፡፡ የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ከአማራ ክልል ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ጋር በመተባበር በደሴ ከተማ የኦሎምፒክ ችቦ ማብራትና ቅብብሎሽ መርሃ-ግብር አካሂዷል፡፡ እንደኮሚቴው አገላለጽ የፓሪስ 2024 ኦሎምፒክ ውድድር በመጪው ሐምሌ ወር እንደሚካሄድም ታወቋል። በውድድሩ ኢትዮጵያ የተሻለ ውጤት እንድታስመዘገብ ከወዲሁ የቅደመ ዝግጅት ስራ እየተከናወነ…

Read More

የኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ሳምንት አውደ-ርዕይ ትውልድ ተሻጋሪ የሆኑ ሥራዎችን ሰንዶ ማስቀመጥ የተቻለበት ነው-አምባሳደር ብርቱካን አያኖ::

የኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ሳምንት አውደ-ርዕይ ለቀጣይ የዲፕሎማሲ ሥራ ትውልድ ተሻጋሪ የሆኑ ሥራዎችን ሰንዶ ማስቀመጥ የተቻለበት መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ ገለጹ። አውደ-ርዕዩ ኢትዮጵያ በዲፕሎማሲው መስክ ብሔራዊ ጥቅሟን አስከብራ ለመዝለቅ ያደረገችውን ጉዞ እና ዲፕሎማሲያዊ ከፍታዋን ያሳየ መሆኑንም ተናግረዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ብርቱካን አያኖ፤ የኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ሳምንት አውደ-ርዕይን አስመልክተው ለመገናኛ ብዙኃን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።…

Read More

መከላከያ ሠራዊቱ ህገ መንግስታዊ ተልዕኮውን በብቃት እየተወጣ ነው – ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ::

መከላከያ ሠራዊቱ ህገ መንግስታዊ ተልዕኮውን በብቃት የመወጣት አኩሪ ተግባሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥል የኢፌዴሪ ጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ አስታወቁ። ብላቴ የሚገኘው የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ ማሰልጠኛ ማዕከል ያሰለጠናቸውን 42ኛ ዙር የኢትዮጵያ ኮርስ መሰረታዊ ኮማንዶ ዛሬ አስመርቋል። በዚህ ወቅት የጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ ባደረጉት ንግግር፤ መከላከያ ሠራዊት የሀገሪቱን…

Read More

በኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነትን በዘላቂነት ማረጋገጥ የሚያስችል አቅም እንዳለ በተግባር ማረጋገጥ ተችሏል – ቢቂላ ሁሪሳ(ዶ/ር)

በኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነትን በዘላቂነት ማረጋገጥ የሚያስችል አቅም እንዳለ በተግባር በማረጋገጥ ተጨባጭ ውጤት መገኘቱን በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ(ዶ/ር) ገለጹ። “ሉዓላዊነት በምርታማነት” በሚል መሪ ሀሳብ የተዘጋጀ የፓናል ውይይት በአዳማ ከተማ እየተካሄደ ነው። የምግብ ሉዓላዊነት የኢትዮጵያ ቁልፍ ጉዳይ መሆኑን ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) መድረኩን በከፈቱበት ወቅት ገለጸዋል። ባለፉት ዓመታት ይህንን ለማረጋገጥ…

Read More