Trendings

በሸካ ዞን የጥምቀት ከተራ በዓል በድምቀት እየተከበረ ይገኛል።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች ዘንድ በድምቀት የሚከበረው የጥምቀት ከተራ በዓል በዞኑ ሁሉም አካባቢዎች በድምቀት መከበር ጀምሯል። የእምነቱ ተከታይ በሆኑ ምዕመናን እና ሌሎች አካላት በመታጀብ ታቦታቱ ከማደሪያ ስፍራቸው በመውጣት ወደ ጥምቀተ ባህር እያመሩ ይገኛሉ። የሸካ ዞን ዋና ከተማና የክልሉ ብዝሃ ማዕከል በሆነችው ቴፒ ከተማ ታቦታቱ ከየአቅጣጫው ታጅበው በድምቀት ወደ ጥምቀተ ባህር እያመሩ ሲሆን በአንድራቻ ወረዳ…

Read More

የመንግስትን ሀብትና ንብረት ከብክነት ለመከላከል ለውስጥ ኦዲት ባለሙያዎች በቂ አቅም መፍጠር እንደሚገባ ተጠቆመ

ከክልሉ ወረዳዎች ለተውጣጡ የኦዲት እና ኢንስፔክሽን ባለሙያዎች ለሁለት ቀናት ሲሰጥ የነበረው የአሰልጣኞች ስልጠና ተጠናቋል። የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ወሰነች ቶማስ እንደተናገሩት፣ስልጠናው የውስጥ ኦዲት እና ኢንስፔክሽን ላይ ያለውን ግንዛቤ በማሳደግ የፋይናንስ ዘርፍ አሰራር ስርዓቱን ለማሳደግ ያለመ ነው ብለዋል። በክልሉ ለሚገኙ የውስጥ ኦዲት ኃላፊዎችና ባለሙያዎች አቅም በመፍጠር ክትትልና ድጋፍ በማድረግና በማስተባበር ያለውን ውስን ሀብት በአግባቡ ስራ…

Read More

የግብርና ሚኒስትር ዶክተር ግርማ አመንቴ ከዓለም ባንክ ዋና ዳይሬክተር ጋር ተወያዩ

የግብርና ሚኒስትር ዶክተር ግርማ አመንቴ ከዓለም ባንክ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ፍሎሪበርት ንጋሩኮ ጋር ተወያይተዋል፡፡ ሚኒስትሩ መንግስት ባለፉት 5 ዓመታት ለግብርናው ዘርፍ ትልቅ ትኩረት በመስጠት ዘርፈ ብዙ ስራዎችን በማከናወን ላይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በዓለም ባንክ የበጀት ድጋፍ ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች በመተግበር ላይ መሆናቸውን ገልጸው፤ ባንኩ ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የምታደርገውን ጥረት ይበልጥ እንዲያግዝ ጠይቀዋል፡፡ ዶክተር…

Read More

ለበጋ መስኖ ስንዴ የምርጥ ዘርና የማዳበሪያ አቅርቦት በስፋት እየተከናወነ ነው – ግብርና ሚኒስቴር

ለ2018 በጀት ዓመት የበጋ መስኖ ስንዴ ምርትና ምርታማነትን የሚያሳድጉ የምርጥ ዘርና የማዳበሪያ አቅርቦት በስፋት እየተከናወነ መሆኑን ግብርና ሚኒስቴር አስታውቋል። ሚኒስቴሩ ከ767 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በማረስ ከዚህ ውስጥም ከ359 ሺህ ሄከታር መሬት በላይ በዘር መሸፈኑን ገልጿል። የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ የአርሶ አደሩን የስራ ባህል በመቀየር በዓመት ከሁለት ጊዜ በላይ እየተመረተ ይገኛል።…

Read More

የብሔራዊ ቤተመንግስት ሙዚየም ለህዝብ ክፍት ሆነ

እድሳት ተደርጎለት ላለፉት 4 ወራት በሙከራ ስራ ላይ የቆየው የብሔራዊ ቤተመንግስት ሙዚየም ከዛሬ ጀምሮ ለህዝብ ክፍት ተደርጓል፡፡ ቤተመንግስቱ ጥንታዊ ተሽከርካሪዎችና መካነ እንስሳትን ጨምሮ በውስጡ በርካታ ታሪካዊ ቅርሶችን የያዘ ሲሆን፥ ደረጃቸውን የጠበቁ ሬስቶራንቶችና ስፓዎች ይገኙበታል፡፡ ሙዚየሙ ክፍት መደረጉን አስመልክተው የብሔራዊ ቤተመንግስት ዋና አስተዳዳሪ አቶ ምትኩ ደሬሳ በሰጡት መግለጫ፥ ቤተመንግስቱ ኢትዮጵያን ከተረጂነት ለማላቀቅ ትልቅ ሚና እንዳለው አንስተዋል፡፡…

Read More

ከማምረት የሚሻገር ዕድል ይዘው የመጡ የመኖ ማቀነባበሪያ ማሽኖች በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል

ሪፖርታዥ ከማምረት የሚሻገር ዕድል ይዘው የመጡ የመኖ ማቀነባበሪያ ማሽኖች በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የአንድ ሀገር ሁለንተናዊ እድገት ከሚያመላክቱ ጉዳዮች አንዱ የዜጎች አካላዊና አዕምሯዊ ጤንነት መረጋገጥ መቻሉ ነው። ከዚህ ጋር በተያያዘ በብዙ ታዳጊ ሀገራት ላይ የሚስተዋለው የመቀንጨር ችግር ከኢትዮጵያ እንዲጠፋ ዘንድ መንግስት የተለያዩ እርምጃዎችን እየወሰደ እንዳለ ማወቅ ተችላሏል። ከእነዚህ የመፍትሔ አቅጣጫዎች አንዱ ዜጎች በፕሮቲን የበለጸጉ…

Read More

ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ለኮንታ ብሔር የዘመን መለወጫ (ህንግጫ) በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ለኮንታ ብሔር የዘመን መለወጫ (ህንግጫ) በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር)፣ የኮንታ ብሔር የዘመን መለወጫ የሆነውን (ህንግጫ) በዓልን ምክንያት በማድረግ ለመላው የብሔሩ ተወላጆች እና ወዳጆች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። ርዕሰ መስተዳድሩ በመልዕክታቸው፣ የህንግጫ በዓል የኮንታ ብሔር ጥንታዊ ባህል፣ እሴትና ማንነት…

Read More

ኢትዮጵያ በዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኤጄንሲ ጉባዔ ላይ እየተሳተፈች ነው::

14ኛው ዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኤጄንሲ ጉባዔ በተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች አቡ ዳቢ በዛሬው ዕለት ተጀምሯል፡፡ በጉባዔው የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ሃብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር ኢ/ር) እና በተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች የኢትዮጵያ አምባሳደር ዑመር ሁሴን (ዶ/ር) ኢትዮጵያን በመወከል ተሳትፈዋል፡፡ በጉባኤው ከታዳሽ ኃይል እና የአየር ንብረት ለውጥ ጋር በተያያዘ በርካታ ሪፖርቶች ቀርበው ውይይት እንደሚደረግባቸው በተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች የኢትዮጵያ ኤምባሲ…

Read More

ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ለ1,447ኛው የኢድ አልፈጥር በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ፣ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች ለ1,447ኛው የኢድ አልፈጥር በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ። ርዕሰ መስተዳድሩ በመልዕክታቸው በዓሉ የሰላም፣ የፍቅርና የመረዳዳት እንዲሆን ምኞታቸውን ገልጸዋል። ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ ባስተላለፉት መልዕክት፣ የኢድ አልፈጥር በዓል የትዕግስት፣ የመስዋዕትነት፣ የርኅራኄ እና የአንድነት እሴቶች የሚጎሉበት ልዩ ወቅት መሆኑን ጠቁመዋል። በተለይም በታላቁ…

Read More

ኢትዮጵያ በዓለም አቀፉ የፓርላማ ኅብረት ስብሰባ ላይ እየተሳተፈች ነው

በፌደሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ አገኘሁ ተሻገር የተመራ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ልዑክ በጄኔቫ እየተካሄደ በሚገኘው 149ኛው ዓለም አቀፍ የፓርላማ ኅብረት ስብሰባ ላይ እየተሳተፈ ነው፡፡ ጉባዔው÷ በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን፣ ሰላምና ፀጥታን በማስፈን እንዲሁም ዴሞክራሲያዊ አሥተዳደርን ማጎልበት በሚሉ ዐበይት ጉዳዮች ላይ በመምከር ውሳኔዎችን እንደሚያሳልፍ ይጠበቃል ተብሏል፡፡ በተጨማሪም ሀገራት ለሚያጋጥሟቸው ተግዳሮቶች መፍትሔ ለማመላከት እና በፓርላማ ደረጃ ሊተገበሩ የሚችሉ የትብብር መፍትሔዎችን…

Read More