Trendings

በሸካ ዞን ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ በትኩረት በሚፈፀሙ ተግባራት ላይ ያተኮረ ውይይት በቴፒ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።

በዞኑ ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ በኢኮኖሚ፣በማህበራዊ፣ በከተማ ልማት እንዲሁም በፖለቲካና ህዝብ ግንኙነት ዘርፎች በልዩ ትኩረት በሚፈፀሙ ተግባራት ዙሪያ ስትራቴጂካዊ ዕቅድ ቀርቦ ውይይት እየተካሄደ ነው። ውጤታማ ተግባራትን በመፈፀም የህብረተሰቡን እርካታ ለማረጋገጥ ብሎም የዞኑን ልማትና እድገት ለማፋጠን በየደረጃው የሚገኙ አመራሮችና ባለድርሻ አካላት ተሳትፎና ርብርብ ወሳኝ መሆኑም ተጠቁሟል። ከተማ ልማት፣ግብርና፣ገቢ አሰባሰብ፣ትምህርትና ጤና ዘርፍ ላይ እመርታ ማስመዝገብ ከርብርብ ማዕከላት ዋነኞቹ…

Read More

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክርቤት 6ኛ ዙር 3ኛ ዓመት 6ኛ መደበኛ ጉባኤ በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡

ምክር ቤቱ መደበኛ ጉባኤውን በታርጫ ከተማ እያካሄደ ሲሆን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ የአስፈጻሚ ተቋማትን የ2016 በጀት ዓመት የአፈጻጸም ሪፖርት እያቀረቡ ነው ፡፡ ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ ለምክርቤቱ ባቀረቡት ሪፖርት በሁሉም የአስተዳደር እርከኖች በተደራጀ መልኩ በመምራትና ውስን የመንግሥት ሃብት ለታለመለት ዓላማ እንዲውል ከማድረግ አንጻር በልዩ ትኩረት ተግባራት መከናወናቸውን አብራርተዋል ፡፡ በዚህም…

Read More

የኢትዮጵያ የሸማቾች መብት ጥበቃ ማህበራት ጥምረት በይፋ ተመሰረተ

በሸማቾች መብት ላይ ትኩረቱን አድርጎ የሚሰራ የኢትዮጵያ የሸማቾች መብት ጥበቃ ማህበራት ጥምረት በይፋ ተመስርቷል፡፡ ጥምረቱ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴዔታ አቶ እንዳለው መኮንን፣ የንግዱ ዘርፍ ባለድርሻ አካላትና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በዛሬው እለት በአዲስ አበባ ከተማ ተመስርቷል፡፡ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴዔታ አቶ እንዳለው መኮንን በዚሁ ወቅት እንዳሉት፣ ሸማቾች በግብይት ስርዓቱ ላይ ትልቁን ድርሻ ይዘው…

Read More

ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ እንዲቻል ጤናው የተጠበቀ ማኅበረሰብ መፍጠር ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ጤና ቢሮ የጤናና ጤና ነክ አገልግሎት ግብዓት ጥራት ቁጥጥር ባለሥልጣን የዓመቱን ዕቅድ አፈጻጸም በታርጫ ከተማ እየገመገመ ነው። በክልሉ ተርጫ ከተማ እየተካሄደ ባለው የዕቅድ አፈጻጸም ላይ በጤና ቢሮ የጤናና ጤና ነክ አገልግሎት ግብዓት ጥራት ቁጥጥር ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ሙሉቀን አሰፋ እንደገለጹት በ2016 በጀት ዓመት በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ጤና ለማስጠበቅ የጋራ…

Read More

ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) የአምራች ኢንዱስትሪ ማምረቻ ማዕከል መርቀው ከፈቱ።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)፥ በኮንታ ዞን አመያ ከተማ በክልሉ መንግሥት የተገነባውን የአምራች ኢንዱስትሪ የማምረቻ ማዕከል መርቀዋል። ፕሮጀክቱ በቀድሞው የደቡብ ክልል ጊዜ ተጀምሮ በተለያዩ ምክንያቶች ግንባታው የተጓተተ ቢሆንም የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምሥረታ ማግስት÷ የክልሉ መንግሥት ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቀው ለኅብረተሰቡ ተገቢውን አግልግሎት እንዲሰጡ በሰጠው ልዩ ትኩረት ተጠናቆ ለምርቃት…

Read More

89ኛው የየካቲት 12 ሰማዕታት መታሰቢያ በዓል ተከበረ

የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማህበር 89ኛውን የየካቲት 12 ሰማዕታት መታሰቢያ በዓል በስድስት ኪሎ በሚገኘው የሰማዕታት መታሰቢያ ሐውልት ፊት ለፊት አክብሯል። በበዓሉ ላይ አባትና እናት አርበኞች በመገኘት የአበባ ጉንጉን በማኖር የሰማዕታቱን መስዋዕትነት ዘክረዋል። የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማህበር ፕሬዝዳንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን፤ ወጣቱ ትውልድ አያትና ቅድመ አያቶቹ ለሀገር ፍቅርና ለአንድነት የከፈሉትን የሕይወት መስዋዕትነት በማሰብ፣ ሀገሩን…

Read More

የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደር አካባቢዎች የመንገድ መሠረተ ልማት ስራዎችን ለማስፋፋት በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ተገለፀ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አርብቶ አደርና ቆላማ አካባቢዎች ጉዳይ ቢሮ በምዕራብ ኦሞ ዞን ከሀዱባ እስከ ኦሞ ኩራዝ ቁጥር 3 የ46 ኪ.ሜትር የመንገድ ከፈታ ስራ ተጠናቆ የክልል፣ የዞን፣ የወረዳ አመራሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ርክብክብ ተደረገ ። በርክብክብ መርሃግብር ላይ የተገኙት የክልሉ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕራግ የመሠረተ ልማት አስተባባሪና የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ…

Read More

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፖሊስ ኮሚሽን በክልል ደረጃ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተወጣጡ አባላት ያለው የወንጀል መከላከል ገለልተኛ አማካሪ ምክር ቤት አቋቋመ

በመድረኩ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ሰብስቤ ሻዎኖ እንደተናገሩት ዛሬ የሚንመሰርተው ክልል አቀፍ ገለልተኛ የወንጀል መከላከል አማካሪ ምክር ቤት ወንጀልን በተደረጀና በተቀናጀ መንገድ ለመከላከል ትልቅ አቅም አለው ብለዋል፡፡ በክልሉ ገለልተኛ የአማካሪ ምክር ቤት መመስረት ያሰፈለገበት ዋና ምክንያት ወንጀል የመከላከሉ ስራ ሁላንታናዊ የዜጎች ተሳትፎ ስለሚያስፈልግና አንዱ የዜጎች ተሳትፎ የሚረጋገጥበት በመሆኑ ነውብለዋል። ገለልተኛ አማካሪ ምክር ቤት ከፖሊስ እና…

Read More

የከተማው የኮሪደር ልማት እንዲፋጠን ድጋፋችንን እናጠናክራለን-የሚዛን አማን ከተማ የነዋሪዎች

በሚዛን አማን ከተማ የተጀመረው የኮሪደር ልማት ሥራ እንዲፋጠን ድጋፋቸውን እንደሚያጠናክሩ የከተማው ነዋሪዎች ገለጹ። ከነዋሪዎቹ መካከል መቶ አለቃ ተስፋዬ ናትናኤል፥ የከተማዋን ገጽታ እየቀየረ ያለውን የኮሪደር ልማት የእግረኛን መንግድ በማስፋትና የመናፈሻ አገልግሎትን ማስፋት ያሰቻለ ሰው ተኮር ፕሮጀክት ነው ብለዋል። ልማቱ በተሳካ ሁኔታ እንዲፋጠን ድጋፋቸውን እንደሚያጠናክሩ አስታውቃዋል። እስከ አሁን የተጠናቀቁ የኮሪደር ልማት ስራዎች የትራንስፖርት እንቅስቃሴን በማቀላጠፍ የተሽከርካሪ አደጋን…

Read More