Trendings

በጎነትን ለማስረጽ እና የአብሮነት እሴቶችን ለማጎልበት የበጎ ፈቃደኛ ወጣቶች ሚና ከፍተኛ ነው ሲሉ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ሴቶች ህፃናት እና ወጣቶች ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ገነት መኩሪያ ገለፁ።

የ2016 የወሰን ተሻጋሪ የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልገሎት ተሳታፊዎች በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ዳውሮ ዞን የተለያዩ በጎ ተግባራትን አከናውነዋል ። በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት ሴቶች ህፃናት እና ወጣቶች ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ገነት መኩሪያ እንደገለፁት ወሰን ተሻጋሪ የክረምት ወራት በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች ሠላምን አስተማማኝና ዘላቂ ለማድረግ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራትን ውጤታማ ለማድረግ ሚናቸው የጎላ ነው…

Read More

በታርጫ ከተማ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በተገኙበት፣ በከፍተኛ ህዝባዊ ንቅናቄ የታጀበ የብልጽግና ፓርቲ የይምረጡኝ ቅስቀሳ እና የድጋፍ ሰልፍ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በተገኙበት፣ የብልጽግና ፓርቲ የይምረጡኝ ቅስቀሳ እና ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ በዳውሮ ዞን ታርጫ ከተማ እየተካሄደ ነው። ይህ ታላቅ የህዝብ ንቅናቄ የለውጡ መንግሥት ላስመዘገባቸው ሁለንተናዊ የልማት ስኬቶችና ለህዝብ ተጠቃሚነት ተጠናክሮ እንዲቀጥል በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ብልፅግና ይሁንታን የሚሰጥ መኾኑ ተመላክቷል። የዞኑ ህዝብ በነቂስ ወጥቶ እያሳየ ያለው ደማቅ…

Read More

በክልሉ በተገኘው ሠላም፣ የገጠርና የከተማ የኢንቨስትመንት ፍሰት በእጅጉ ጨምሯል፦ አቶ አንድነት አሸናፊ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ሠላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ “ዘላቂ ሠላም ለሁለንተናዊ ብልፅግና” በሚል መር ቃል የ2016 ዓ/ም ዕቅድ አፈጻጸምና የ2017 በጀት ዓመት ጠቋሚ ዕቅድ የሴክተር ጉባኤ በቦንጋ ከተማ እያካሄደ ይገኛል። በክልሉ ዘላቂ ሠላምና በማስፈን ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ በ2016 በጀት ዓመት የባለድርሻ አካላት በማሳተፍ በተሰራው ስራ አመርቂ ውጤት መመዝገብ ነው የክልሉ ሠላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ…

Read More

የደቡብ ሞዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዓመታዊ የምርምር ኮንፈረንስ ግምገማ በቦንጋ ከተማ እያካሄደ ይገኛል።

በምርምር ኮንፈረንሱ የክልሉ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የኢትዮጵያ ግብር ምርምር ኢንስቲትዩት ተወካዮች፣ የምርምር ስራዎቻቸውን የሚያቀርቡ የተለያዩ ተመራማሪዎች፣ በክልሉ የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ተወካዮች እና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል። በምርምር ኮንፈረንሱ ላይ በተለያዩ ተመራማሪዎች የተሰሩ የምርምር ስራዎች ግምገማ እንዲሁም የምርምር ስራዎች ኢግዚቢሽን እንደሚካሄድ ከወጣሁ መርሀግብር መመልከት ተችሏል። በዕድገቱ በዛብህ

Read More

በክልሉ ከ2.4 ሚሊዮን በላይ የኅብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ለማከናወን የቅድመ ዝግጅት ሥራ መጠናቀቁ ተገለጸ።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ በበጎ ፈቃድ ስታንዳርድ እና ትመና ላይ ለዞን አመራሮች እና ባለሙያዎች ስልጠና በቦንጋ ከተማ እየሰጠ ይገኛል። በዘንድሮው የክረምት ወጣቶች በጎ ፍቃድ አግልግሎት ከ2.4 ሚሊዮን በላይ የኅብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ የሚያደርግ የበጎ ፍቃድ አግልግሎት ለማከናወን የቅድመ ዝግጅት ሥራ መጠናቀቁን ነው የክልሉ የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ ምክትል ኃላፊ ወ/ሮ…

Read More

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ኢትዮጵያዊያን በላብና በደማቸው ያጸኑት የወል ቅርስ ነው:- ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ መላው ኢትዮጵያዊያን ተባብረው በላብና በደማቸው ያፀኑት የወል ቅርስ መሆኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ገለጹ። የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ በስኬት መጠናቀቅን አስመልከተው በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል፣ በቦንጋ ከተማ የተካሄደው ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ በተለያዩ ትዕይንቶች ታጅቦ በስኬት ተጠናቋል። በህዝባዊ ሰልፉ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የክልሉ…

Read More

5ኛው የፓኪስታን-አፍሪካ የንግድ ልማት ጉባኤና አውደ ርዕይ በአዲስ አበባ ይካሄዳል

5ኛው የፓኪስታን-አፍሪካ የንግድ ልማት ጉባኤና አውደ ርዕይ ከግንቦት 7 እስከ 9/2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሚሊኒየም አዳራሽ እንደሚካሄድ በኢትዮጵያ የፓኪስታን አምባሳደር አቲፍ ሸሪፍ ሚያን ገለጹ። አምባሳደሩ በሰጡት መግለጫ፥ በንግድ ልማት ጉባኤና አውደ ርዕዩ ላይ ከ100 በላይ የፓኪስታን አምራች ድርጅቶች ይሳተፋሉ ብለዋል። ከአፍሪካ ሀገራት ጋር የንግድ ትስስርን የሚያጠናክሩ የሕክምና መድኃኒት ምርትና መሣሪያዎች፣ የውበትና ቆዳ እንክብካቤ ውጤቶች፣ የጨርቃጨርቅና…

Read More

ክልሉ ያለዉን እምቅ አቅም ተጠቅሞ በዜጎች ስራ ዕድል ፈጠራ ላይ ትኩረት ማድረግ አለበት:-የሱፐርቪዥን ቡድን::

የኢፌዲሪ ሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሱፐርቪዥን ቡድን ላለፉት 10 ቀናት በክልሉ ያካሄደውን ድጋፋዊ ሱፐርቪዥን ግብረ- መልስ ማጠቃለያ ውይይት በቦንጋ ከተማ አካሂዷል፡፡ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሰለሞን ሶካ በክልሉ በወጣቶች ስራ ዕድል ፈጠራ ዘርፍ የተሰሩ የተገኙ ውጤቶች ለማስቀጠል ክህሎት መር ተቋማዊ ግንባታ በማጠናከር በየአካባቢ ተገንብተው ወደስራ ያልገቡ የማምራቸ እና መሸጫ ሼዶችን አጠናቆ ወደ ስራ ማስገባት…

Read More

“በትግራይ ምድር አንድም ጥይት የመተኮስ ፍላጎት የለንም”፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የመንግስትን የ2017 የዕቅድ አፈጻጸም አስመልክቶ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እየሰጡ ነው። በእኛ በኩል በትግራይ ምድር አንድም ጥይት የመተኮስ ፍላጎት የለንም ከቻልን የማልማት ፍላጎት ነው ያለን ሲሉ ተናግረዋል፡፡ በትግራይ ክልል ቴሌኮም፣ ባንክ፣ መብራትና ፋብሪካዎች ስራ መጀመራቸውን እና መንግስት መቋቋሙን አስታውቀዋል፡፡ ተፈናቃይን በሚመለከት ራያ 100 በመቶ መመለሳቸውን ገልጸው፤ ምን ቀረ…

Read More